La sourate Al-Ala en Amharique
سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى(1) ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ |
الَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ(2) የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡ |
وَالَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ(3) የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡ |
وَالَّذِي أَخْرَجَ الْمَرْعَىٰ(4) የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡ |
فَجَعَلَهُ غُثَاءً أَحْوَىٰ(5) (ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡ |
سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰ(6) (ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡ |
إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ إِنَّهُ يَعْلَمُ الْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ(7) አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡ |
وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَىٰ(8) ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡ |
فَذَكِّرْ إِن نَّفَعَتِ الذِّكْرَىٰ(9) ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡ |
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخْشَىٰ(10) (አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡ |
وَيَتَجَنَّبُهَا الْأَشْقَى(11) መናጢውም ይርቃታል፡፡ |
الَّذِي يَصْلَى النَّارَ الْكُبْرَىٰ(12) ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡ |
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَىٰ(13) ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡ |
قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ(14) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡ |
وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّىٰ(15) የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡ |
بَلْ تُؤْثِرُونَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا(16) ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡ |
وَالْآخِرَةُ خَيْرٌ وَأَبْقَىٰ(17) መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡ |
إِنَّ هَٰذَا لَفِي الصُّحُفِ الْأُولَىٰ(18) ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡ |
صُحُفِ إِبْرَاهِيمَ وَمُوسَىٰ(19) በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡ |
Plus de sourates en Amharique :
Téléchargez la sourate avec la voix des récitants du Coran les plus célèbres :
Téléchargez le fichier mp3 de la sourate Al-Ala : choisissez le récitateur pour écouter et télécharger la sourate Al-Ala complète en haute qualité.
Ahmed Al Ajmy
Bandar Balila
Khalid Al Jalil
Saad Al Ghamdi
Saud Al Shuraim
Abdul Basit
Abdul Rashid Sufi
Abdullah Basfar
Abdullah Al Juhani
Fares Abbad
Maher Al Muaiqly
Al Minshawi
Al Hosary
Mishari Al-afasi
Yasser Al Dosari
Donnez-nous une invitation valide




