PDF —
45 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ ቃፍ pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ ቃፍ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ ቃፍ ትርጉም. ሱረቱ ቃፍ (Meccan) 45 አንቀጽ.



45 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﭑﭒﭓﭔﭕ
50:1 ቀ (ቃፍ) በተከበረው ቁርኣን እምላለሁ (በሙሐመድ አላመኑም)፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
50:2 ይልቁንም ከነሱ ጎሳ የኾነ አስፈራሪ ስለ መጣላቸው ተደነቁ፡፡ ከሓዲዎቹም «ይህ አስደናቂ ነገር ነው» አሉ፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
50:3 «በሞትንና ዐፈር በኾን ጊዜ (እንመለሳለን?) ይህ ሩቅ የኾነ መመለስ ነው፤» (አሉ)፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
50:4 ከእነርሱ (አካል) ምድር የምታጎድለውን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ እኛም ዘንድ ጠባቂ መጽሐፍ አልለ፡፡
ﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
50:5 (አልተመለከቱም)፡፡ ይልቁንም በቁርኣን በመጣላቸው ጊዜ አስተባበሉ፡፡ እነርሱም በተማታ ነገር ውሰጥ ናቸው፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
50:6 ወደ ሰማይም ከበላያቸው ስትኾን ለእርሷ ምንም ቀዳዳዎች የሌሏት ኾና እንዴት እንደ ገነባናትና (በከዋክብት) እንዳጌጥናት አልተመለከቱምን?
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
50:7 ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በእርሷም ውስጥ ጋራዎችን ጣልንባት፡፡ በውስጧም ከሚያስደስት ዓይነት ሁሉ አበቀልን፡፡
ﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
50:8 (ይህንን ያደረግነው) ተመላሽ ለኾነ ባሪያ ሁሉ ለማሳየትና ለማስገንዘብ ነው፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
50:9 ከሰማይም ብሩክን ውሃ አወረድን፡፡ በእርሱም አትክልቶችንና የሚታጨድን (አዝመራ) ፍሬ አበቀልን፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
50:10 ዘምባባንም ረዣዢም ለእርሷ የተደራረበ እንቡጥ ያላት ስትኾን (አበቀልን)፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
50:11 ለባሮቹ ሲሳይ ትኾን ዘንድ (አዘጋጀናት)፡፡ በእርሱም የሞተችን አገር ሕያው አደረግንበት፡፡ (ከመቃብር) መውጣትም እንደዚሁ ነው፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
50:12 ከእነርሱ በፊት የኑሕ ሕዝቦችና የረሰስ ሰዎች፤ ሰሙድም አስተባበሉ፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨ
50:13 ዓድም ፈርዖንም፤ የሉጥ ወንድሞችም፤
ﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
50:14 የአይከት ሰዎችም የቱብበዕ ሕዝቦችም ሁሉም መልከተኞቹን አስተባበሉ፡፡ ዛቻዬም ተረጋገጠባቸው፡፡
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿ
50:15 በፊተኛው መፍጠር ደከምን? በእውነቱ እነርሱ ከአዲስ መፍጠር በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
50:16 ሰውንም ነፍሱ (በሐሳቡ) የምታጫውተውን የምናውቅ ስንኾን በእርግጥ ፈጠርነው፤ እኛም ከደም ጋኑ ጅማት ይበልጥ ወደርሱ ቅርብ ነን፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
50:17 ሁለቱ ቃል ተቀባዮች (መላእክት) ከቀኝና ከግራ ተቀማጮች ኾነው በሚቀበሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
50:18 ከቃል ምንም አይናገርም በአጠገቡ ተጠባባቂና ዝግጁ የኾኑ (መላእክት) ያሉበት ቢኾን እንጅ፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽ
50:19 የሞትም መከራ እውነቱን ነገር ታመጣለች፡፡ (ሰው ሆይ)፡- «ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበርከው ነው» (ይባላል)፡፡
ﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
50:20 በቀንዱም ውስጥ ይንነፋል፡፡ ያ (ቀን) የዛቻው (መፈጸሚያ) ቀን ነው፡፡
ﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
50:21 ነፍስም ሁሉ ከእርሷ ጋር ነጂና መስካሪ ያለባት ኾና ትመጣለች፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
50:22 «ከዚህ ነገር በእርግጥ በዝንጋቴ ውስጥ ነበርክ፡፡ ሺፋንህንም ካንተ ላይ ገለጥንልህ፡፡ ስለዚህ ዛሬ ዓይንህ ስለታም ነው» (ይባላል)፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
50:23 ቁራኛውም (መልአክ) «ይህ ያ እኔ ዘንድ ያለው ቀራቢ ነው» ይላል፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
50:24 «ሞገደኛ ከሓዲን ሁሉ በገሀነም ውስጥ ጣሉ፡፡»
ﮨﮩﮪﮫﮬ
50:25 «ለበጎ ሥራ ከልካይ፣ በዳይ፣ ተጠራጣሪ የኾነን ሁሉ፤» (ጣሉ)፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘ
50:26 «ያንን ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ ያደረገውን በብርቱ ቅጣት ውስጥ ጣሉት፤» (ይባላል)፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
50:27 ቁራኛው (ሰይጣን) «ጌታችን ሆይ! እኔ አላሳሳትኩትም፡፡ ግን (ራሱ) በሩቅ ስሕተት ውስጥ ነበር» ይላል፡፡
ﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭ
50:28 (አላህ) «ወደእናንተ ዛቻን በእርግጥ ያስቀደምኩ ስኾን እኔ ዘንድ አትጨቃጨቁ» ይላቸዋል፡፡
ﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵﯶ
50:29 «ቃሉ እኔ ዘንድ አይለወጥም፡፡ እኔም ለባሮቼ ፈጽሞ በዳይ አይደለሁም» (ይላቸዋል)፡፡
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
50:30 ለገሀነም «ሞላሽን? የምንልበትንና ጭማሪ አለን? የምትልበትን ቀን» (አስጠንቅቃቸው)፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆ
50:31 ገነትም አላህን ለፈሩት እሩቅ ባልኾነ ስፍራ ትቅቀረባለች፡፡
ﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
50:32 «ይህ ወደ አላህ ተመላሽና (ሕግጋቱን) ጠባቂ ለኾነ ሁሉ የተቀጠራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
50:33 «አልረሕማንን በሩቁ ኾኖ ለፈራና በንጹሕ ልብ ለመጣ» (ትቅቀረባለች)፡፡
ﰖﰗﰘﰙﰚﰛﰜ
50:34 «በሰላም ግቧት ይህ የመዘውተሪያ ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﰝﰞﰟﰠﰡﰢﰣ
50:35 ለነርሱ በውስጧ ሲኾኑ የሚሹት ሁሉ አልላቸው፡፡ እኛም ዘንድ ጭማሪ አልለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
50:36 ከእነርሱም (ከቁረይሾች) በፊት ከክፍለ ዘመናት ሕዝቦች ብዙዎችን እነርሱ በኀያልነት ከእነርሱ ይበልጥ የበረቱ የኾኑትን (ማምለጫ ፍለጋ) በየአገሮቹም የመረመሩትን አጥፍተናል፡፡ ማምለጫ አለን?
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
50:37 በዚህ ውሰጥ ለእርሱ ልብ ላለው ወይም እርሱ (በልቡ) የተጣደ ኾኖ (ወደሚነበብለት) ጆሮውን ለጣለ ሰው ግሳጼ አለበት፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
50:38 ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
50:39 በሚሉትም ላይ ታገሥ፤ ጌታህንም ከማመስገን ጋር ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ከመግባቷም በፊት አወድሰው፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
50:40 ከሌሊቱም አወድሰው ከስግደቶችም በኋላዎች (አወድሰው)፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
50:41 (የሚነገርህን) አዳምጥም፡፡ ጠሪው ከቅርብ ስፍራ በሚጠራበት ቀን (ከመቃብራቸው ይወጣሉ)፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
50:42 ጩኸቲቱን በእውነት የሚሰሙበት ቀን ያ (ከመቃብር) የመውጫው ቀን ነው፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
50:43 እኛ እኛው ሕያው እናደርጋለን፡፡ እንገድላለንም፡፡ መመለሻም ወደእኛ ብቻ ነው፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
50:44 የሚፈጥኑ ኾነው ምድር ከእነርሱ ላይ የምትሰነጣጠቅበት ቀን (የመውጫው ቀን ነው)፡፡ ይህ በእኛ ላይ ገር የኾነ መሰብሰብ ነው፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
50:45 እኛ የሚሉትን ሁሉ ዐዋቂ ነን፡፡ አንተም በእነርሱ ላይ አስገዳጅ አይደለህም፡፡ ስለዚህ ዛቻየን የሚፈራን ሰው በቁርኣን አስታውስ፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Wednesday, September 9, 2026

Don't forget us in your sincere prayers