ሱረቱ አር-ራህማን ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አር-ራህማንን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (78 አንቀጽ — مدنية). አር-ራህማን ስሙ, አር-ራህማን ትርጉም, አር-ራህማን mp3, አር-ራህማን pdf.

ሱረቱ አር-ራህማንን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
الرَّحْمَٰنُ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
አል-ረሕማን፤
عَلَّمَ الْقُرْآنَ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
خَلَقَ الْإِنسَانَ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ሰውን ፈጠረ፡፡
عَلَّمَهُ الْبَيَانَ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
መናገርን አስተማረው፡፡
الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ بِحُسْبَانٍ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
وَالسَّمَاءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ الْمِيزَانَ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
أَلَّا تَطْغَوْا فِي الْمِيزَانِ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
وَأَقِيمُوا الْوَزْنَ بِالْقِسْطِ وَلَا تُخْسِرُوا الْمِيزَانَ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
وَالْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
فِيهَا فَاكِهَةٌ وَالنَّخْلُ ذَاتُ الْأَكْمَامِ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
وَالْحَبُّ ذُو الْعَصْفِ وَالرَّيْحَانُ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
خَلَقَ الْإِنسَانَ مِن صَلْصَالٍ كَالْفَخَّارِ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
وَخَلَقَ الْجَانَّ مِن مَّارِجٍ مِّن نَّارٍ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
رَبُّ الْمَشْرِقَيْنِ وَرَبُّ الْمَغْرِبَيْنِ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
مَرَجَ الْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌ لَّا يَبْغِيَانِ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
يَخْرُجُ مِنْهُمَا اللُّؤْلُؤُ وَالْمَرْجَانُ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
وَلَهُ الْجَوَارِ الْمُنشَآتُ فِي الْبَحْرِ كَالْأَعْلَامِ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
كُلُّ مَنْ عَلَيْهَا فَانٍ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
وَيَبْقَىٰ وَجْهُ رَبِّكَ ذُو الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
يَسْأَلُهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ كُلَّ يَوْمٍ هُوَ فِي شَأْنٍ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
سَنَفْرُغُ لَكُمْ أَيُّهَ الثَّقَلَانِ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
يَا مَعْشَرَ الْجِنِّ وَالْإِنسِ إِنِ اسْتَطَعْتُمْ أَن تَنفُذُوا مِنْ أَقْطَارِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ فَانفُذُوا ۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلْطَانٍ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
يُرْسَلُ عَلَيْكُمَا شُوَاظٌ مِّن نَّارٍ وَنُحَاسٌ فَلَا تَنتَصِرَانِ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فَإِذَا انشَقَّتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ وَرْدَةً كَالدِّهَانِ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فَيَوْمَئِذٍ لَّا يُسْأَلُ عَن ذَنبِهِ إِنسٌ وَلَا جَانٌّ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
يُعْرَفُ الْمُجْرِمُونَ بِسِيمَاهُمْ فَيُؤْخَذُ بِالنَّوَاصِي وَالْأَقْدَامِ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
هَٰذِهِ جَهَنَّمُ الَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا الْمُجْرِمُونَ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
يَطُوفُونَ بَيْنَهَا وَبَيْنَ حَمِيمٍ آنٍ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
وَلِمَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ جَنَّتَانِ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
ذَوَاتَا أَفْنَانٍ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِمَا عَيْنَانِ تَجْرِيَانِ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِمَا مِن كُلِّ فَاكِهَةٍ زَوْجَانِ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ فُرُشٍ بَطَائِنُهَا مِنْ إِسْتَبْرَقٍ ۚ وَجَنَى الْجَنَّتَيْنِ دَانٍ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِنَّ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 57
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
كَأَنَّهُنَّ الْيَاقُوتُ وَالْمَرْجَانُ ۝٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 58
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 59
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ ۝٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 60
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 61
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ ۝٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 62
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 63
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
مُدْهَامَّتَانِ ۝٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 64
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 65
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِمَا عَيْنَانِ نَضَّاخَتَانِ ۝٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 66
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 67
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِمَا فَاكِهَةٌ وَنَخْلٌ وَرُمَّانٌ ۝٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 68
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 69
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
فِيهِنَّ خَيْرَاتٌ حِسَانٌ ۝٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 70
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 71
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
حُورٌ مَّقْصُورَاتٌ فِي الْخِيَامِ ۝٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 72
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 73
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
لَمْ يَطْمِثْهُنَّ إِنسٌ قَبْلَهُمْ وَلَا جَانٌّ ۝٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 74
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 75
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
مُتَّكِئِينَ عَلَىٰ رَفْرَفٍ خُضْرٍ وَعَبْقَرِيٍّ حِسَانٍ ۝٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 76
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ ۝٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 77
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
تَبَارَكَ اسْمُ رَبِّكَ ذِي الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ ۝٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 78
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
← 54 አር-ራህማን (55/114) 56 →
ማንበብ ሱረቱ አር-ራህማን አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

55الرحمن Ar-Rahman 📚 78 አንቀጽ مدنية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አር-ራህማን — 78 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers