ሱረቱ አን-ነበእ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አን-ነበእን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (40 አንቀጽ — مكية). አን-ነበእ ስሙ, አን-ነበእ ትርጉም, አን-ነበእ mp3, አን-ነበእ pdf.

ሱረቱ አን-ነበእን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
عَمَّ يَتَسَاءَلُونَ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
عَنِ النَّبَإِ الْعَظِيمِ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
الَّذِي هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
كَلَّا سَيَعْلَمُونَ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ مِهَادًا ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
وَالْجِبَالَ أَوْتَادًا ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
وَخَلَقْنَاكُمْ أَزْوَاجًا ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًا ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا اللَّيْلَ لِبَاسًا ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا النَّهَارَ مَعَاشًا ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًا شِدَادًا ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
وَجَعَلْنَا سِرَاجًا وَهَّاجًا ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
وَأَنزَلْنَا مِنَ الْمُعْصِرَاتِ مَاءً ثَجَّاجًا ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
لِّنُخْرِجَ بِهِ حَبًّا وَنَبَاتًا ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
وَجَنَّاتٍ أَلْفَافًا ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
إِنَّ يَوْمَ الْفَصْلِ كَانَ مِيقَاتًا ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
يَوْمَ يُنفَخُ فِي الصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًا ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
وَفُتِحَتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ أَبْوَابًا ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
وَسُيِّرَتِ الْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًا ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
لِّلطَّاغِينَ مَآبًا ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
لَّابِثِينَ فِيهَا أَحْقَابًا ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًا وَلَا شَرَابًا ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
إِلَّا حَمِيمًا وَغَسَّاقًا ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
جَزَاءً وِفَاقًا ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا لَا يَرْجُونَ حِسَابًا ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا كِذَّابًا ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ كِتَابًا ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
فَذُوقُوا فَلَن نَّزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
حَدَائِقَ وَأَعْنَابًا ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًا ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
وَكَأْسًا دِهَاقًا ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
لَّا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا كِذَّابًا ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
جَزَاءً مِّن رَّبِّكَ عَطَاءً حِسَابًا ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
رَّبِّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا الرَّحْمَٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًا ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
يَوْمَ يَقُومُ الرُّوحُ وَالْمَلَائِكَةُ صَفًّا ۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَٰنُ وَقَالَ صَوَابًا ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الْحَقُّ ۖ فَمَن شَاءَ اتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِ مَآبًا ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
إِنَّا أَنذَرْنَاكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَابًا ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
← 77 አን-ነበእ (78/114) 79 →
ማንበብ ሱረቱ አን-ነበእ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

78النبأ An-Naba 📚 40 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አን-ነበእ — 40 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers