ሱረቱ አል-ሂጅር pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አል-ሂጅር pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ሂጅር ትርጉም. ሱረቱ አል-ሂጅር (Meccan) 99 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አል-ሂጅር

ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
15:1
አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
15:2
እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
15:3
ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
15:4
ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
15:5
ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
15:6
«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
15:7
«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
15:8
መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
15:9
እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
15:10
ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
15:11
ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
15:12
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
15:13
በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨ
15:14
በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤
ﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
15:15
«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
15:16
በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
15:17
ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
15:18
ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
15:19
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻ
15:20
በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
15:21
መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡
ﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
15:22
ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
15:23
እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
15:24
ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
15:25
ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
15:26
ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
15:27
ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
15:28
ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
15:29
(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
15:30
መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
15:31
ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙ
15:32
(አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
15:33
«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
15:34
(አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
15:35
«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
15:36
«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾ
15:37
(አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃ
15:38
«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
15:39
(ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»
ﮏﮐﮑﮒﮓ
15:40
«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
15:41
(አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
15:42
«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»
ﮦﮧﮨﮩﮪ
15:43
«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
15:44
«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
15:45
«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ﯛﯜﯝﯞ
15:46
«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
15:47
«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
15:48
«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»
ﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
15:49
ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
15:50
ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅ
15:51
ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚ
15:52
በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
15:53
«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
15:54
«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
15:55
«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡
ﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
15:56
«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
15:57
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
15:58
«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
15:59
«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
15:60
«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
15:61
መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤
ﮞﮟﮠﮡﮢ
15:62
(ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡
ﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
15:63
«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯ
15:64
«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
15:65
ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
15:66
ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮ
15:67
የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
15:68
(ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
15:69
«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
15:70
«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
15:71
(ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
15:72
በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡
ﭞﭟﭠﭡ
15:73
ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
15:74
ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
15:75
በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡
ﭱﭲﭳﭴ
15:76
እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
15:77
በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
15:78
እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
15:79
ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
15:80
የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
15:81
ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
15:82
ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡
ﮚﮛﮜﮝ
15:83
ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
15:84
ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
15:85
ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
15:86
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
15:87
ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡
ﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
15:88
ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
15:89
በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿ
15:90
(ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
15:91
(እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡
ﭖﭗﭘﭙ
15:92
በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤
ﭚﭛﭜﭝ
15:93
ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
15:94
የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡
ﭥﭦﭧﭨ
15:95
ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
15:96
(እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
15:97
አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
15:98
ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
15:99
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







