ሱረቱ አል-ሂጅር
PDF —
99 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ አል-ሂጅር pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ አል-ሂጅር pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ሂጅር ትርጉም. አል-ሂጅር (Meccan) 99 አንቀጽ.



ሱረቱ አል-ሂጅር
99 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨ
በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤
ﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻ
በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡
ﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙ
(አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
(አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾ
(አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃ
«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
(ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»
ﮏﮐﮑﮒﮓ
«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
(አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»
ﮦﮧﮨﮩﮪ
«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ﯛﯜﯝﯞ
«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»
ﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚ
በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡
ﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤
ﮞﮟﮠﮡﮢ
(ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡
ﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯ
«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮ
የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
(ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
(ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡
ﭞﭟﭠﭡ
ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡
ﭱﭲﭳﭴ
እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡
ﮚﮛﮜﮝ
ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡
ﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿ
(ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
(እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡
ﭖﭗﭘﭙ
በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤
ﭚﭛﭜﭝ
ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡
ﭥﭦﭧﭨ
ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
(እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers