ሱረቱ አል-ፈጅር ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ፈጅርን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (30 አንቀጽ — مكية). አል-ፈጅር ስሙ, አል-ፈጅር ትርጉም, አል-ፈጅር mp3, አል-ፈጅር pdf.

ሱረቱ አል-ፈጅርን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَالْفَجْرِ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
በጎህ እምላለሁ፡፡
وَلَيَالٍ عَشْرٍ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
وَالشَّفْعِ وَالْوَتْرِ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
وَاللَّيْلِ إِذَا يَسْرِ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
هَلْ فِي ذَٰلِكَ قَسَمٌ لِّذِي حِجْرٍ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
إِرَمَ ذَاتِ الْعِمَادِ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
الَّتِي لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِي الْبِلَادِ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
وَثَمُودَ الَّذِينَ جَابُوا الصَّخْرَ بِالْوَادِ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
وَفِرْعَوْنَ ذِي الْأَوْتَادِ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
الَّذِينَ طَغَوْا فِي الْبِلَادِ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
فَأَكْثَرُوا فِيهَا الْفَسَادَ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
فَصَبَّ عَلَيْهِمْ رَبُّكَ سَوْطَ عَذَابٍ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
إِنَّ رَبَّكَ لَبِالْمِرْصَادِ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
فَأَمَّا الْإِنسَانُ إِذَا مَا ابْتَلَاهُ رَبُّهُ فَأَكْرَمَهُ وَنَعَّمَهُ فَيَقُولُ رَبِّي أَكْرَمَنِ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
وَأَمَّا إِذَا مَا ابْتَلَاهُ فَقَدَرَ عَلَيْهِ رِزْقَهُ فَيَقُولُ رَبِّي أَهَانَنِ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَل لَّا تُكْرِمُونَ الْيَتِيمَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
وَلَا تَحَاضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ الْمِسْكِينِ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
وَتَأْكُلُونَ التُّرَاثَ أَكْلًا لَّمًّا ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
وَتُحِبُّونَ الْمَالَ حُبًّا جَمًّا ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
كَلَّا إِذَا دُكَّتِ الْأَرْضُ دَكًّا دَكًّا ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
وَجَاءَ رَبُّكَ وَالْمَلَكُ صَفًّا صَفًّا ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
وَجِيءَ يَوْمَئِذٍ بِجَهَنَّمَ ۚ يَوْمَئِذٍ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ وَأَنَّىٰ لَهُ الذِّكْرَىٰ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
فَيَوْمَئِذٍ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُ أَحَدٌ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُ أَحَدٌ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
يَا أَيَّتُهَا النَّفْسُ الْمُطْمَئِنَّةُ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
ارْجِعِي إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةً مَّرْضِيَّةً ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
فَادْخُلِي فِي عِبَادِي ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
وَادْخُلِي جَنَّتِي ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
← 88 አል-ፈጅር (89/114) 90 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ፈጅር አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

89الفجر Al-Fajr 📚 30 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ፈጅር — 30 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers