ሱረቱ አዝ-ዛሪያት
PDF —
Built right in your browser — download starts automatically
ሱረቱ አዝ-ዛሪያት pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አዝ-ዛሪያት pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አዝ-ዛሪያት ትርጉም. አዝ-ዛሪያት (Meccan) 60 አንቀጽ.
Related
- አዝ-ዛሪያት ትርጉምአማርኛ
- አዝ-ዛሪያት mp3ስሙ
- Quran Index አማርኛ114
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አዝ-ዛሪያት

ﯤﯥﯦ
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡
ﯧﯨﯩ
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡
ﯪﯫﯬ
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡
ﯭﯮﯯ
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡
ﯰﯱﯲﯳ
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡
ﯴﯵﯶﯷ
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
ﭑﭒﭓﭔ
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
ﭕﭖﭗﭘﭙ
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞ
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡
ﭟﭠﭡ
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬ
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡
ﮓﮔﮕﮖ
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘ
በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን?
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃ
ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡
ﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
(እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡»
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡
ﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡
ﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗﰘﰙ
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡
ቅዱስ ቁርኣን
Tuesday, August 18, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







