ሱረቱ አዝ-ዛሪያት pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አዝ-ዛሪያት pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አዝ-ዛሪያት ትርጉም. ሱረቱ አዝ-ዛሪያት (Meccan) 60 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አዝ-ዛሪያት

ﯤﯥﯦ
51:1
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡
ﯧﯨﯩ
51:2
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡
ﯪﯫﯬ
51:3
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡
ﯭﯮﯯ
51:4
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡
ﯰﯱﯲﯳ
51:5
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡
ﯴﯵﯶﯷ
51:6
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
ﭑﭒﭓﭔ
51:7
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
ﭕﭖﭗﭘﭙ
51:8
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞ
51:9
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡
ﭟﭠﭡ
51:10
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
51:11
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬ
51:12
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
51:13
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
51:14
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
51:15
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
51:16
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
51:17
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡
ﮓﮔﮕﮖ
51:18
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
51:19
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
51:20
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
51:21
በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
51:22
ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘ
51:23
በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
51:24
የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን?
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
51:25
በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
51:26
ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
51:27
ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃ
51:28
ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡
ﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
51:29
ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
51:30
እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
51:31
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
51:32
(እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡»
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
51:33
በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
51:34
በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
51:35
ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
51:36
በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
51:37
በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
51:38
በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
51:39
ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
51:40
እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡
ﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
51:41
በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
51:42
በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
51:43
በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
51:44
ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
51:45
መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
51:46
የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
51:47
ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺ
51:48
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
51:49
ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
51:50
«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡
ﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗﰘﰙ
51:51
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
51:52
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
51:53
በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
51:54
ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
51:55
ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
51:56
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
51:57
ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
51:58
አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
51:59
ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
51:60
ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







