ሱረቱ አድ-ዱኻን pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አድ-ዱኻን pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አድ-ዱኻን ትርጉም. ሱረቱ አድ-ዱኻን (Meccan) 59 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አድ-ዱኻን

ﭑﭒ
44:1
ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡
ﭓﭔﭕ
44:2
አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟ
44:3
እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡
ﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
44:4
በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
44:5
ከእኛ ዘንድ የኾነ ትእዛዝ ሲኾን (አወረድነው)፡፡ እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
44:6
ከጌታህ በኾነው ችሮታ (ተላኩ)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
44:7
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ከኾነው (ተላኩ)፡፡ የምታረጋግጡ እንደኾናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መኾኑን እወቁ)፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
44:8
ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ያደርጋል፡፡ ይገድላልም፡፡ ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
44:9
በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲኾኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
44:10
ሰማይም በግልጽ ጭስ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
44:11
ሰዎችን የሚሸፍን (በኾነ ጭስ) ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
44:12
«ጌታችን ሆይ! ከእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን፡፡ እኛ አማኞች እንኾናለንና» (ይላሉም)፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
44:13
(ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መግገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል? አስረጅ መልክተኛ የመጣቸው ሲኾን (የካዱም ሲኾኑ)፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗ
44:14
ከዚያም ከእርሱ የዞሩ፤ (ከሰው) «የተሰተማረ ዕብድ ነው» ያሉም ሲኾኑ፡፡
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
44:15
እኛ ቅጣቱን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን፡፡ እናንተ (ወደ ክህደታችሁ) በእርግጥ ተመላሾች ናችሁ፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
44:16
ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን፤ እኛ ተበቃዮች ነን፡፡
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
44:17
ከእነርሱም በፊት የፈርዖንን ሕዝቦች በእርግጥ ሞከርን፡፡ ክቡር መልእክተኛም መጣላቸው፡፡
ﯱﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
44:18
«የአላህን ባሮች ወደኔ አድርሱ፡፡ እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝና፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
44:19
«በአላህም ላይ አትኩሩ፡፡ እኔ ግልጽ የኾነን አስረጅ ያመጣሁላችሁ ነኝና (በማለት መጣላቸው)፡፡
ﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
44:20
«እኔም እንዳትወግሩኝ በጌታየና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
44:21
«በእኔም ባታምኑ ራቁኝ» (ተዉኝ አለ)፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
44:22
ቀጥሎም (ስለ ዛቱበት) «እነዚህ አመጸኞች ሕዝቦች ናቸው» (አጥፋቸው) ሲል ጌታውን ለመነ፡፡
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
44:23
(ጌታው) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና፡፡
ﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽ
44:24
«ባሕሩንም የተከፈተ ኾኖ ተወው፡፡ እነርሱ የሚሰጥጠሙ ሰራዊት ናቸውና» (አለው)፡፡
ﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
44:25
ከአትክልቶችና ከምንጮችም ብዙ ነገሮችን ተዉ፡፡
ﮄﮅﮆﮇ
44:26
ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም፡፡
ﮈﮉﮊﮋﮌ
44:27
በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ተዉ)፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
44:28
(ነገሩ) እንደዚሁ ኾነ፡፡ ሌሎችንም ሕዝቦች አወረስናት፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
44:29
ሰማይና ምድርም በእነርሱ ላይ አላለቀሱም፡፡ የሚቆዩም አልነበሩም፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
44:30
የእስራኤልንም ልጆች አዋራጅ ከኾነ ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
44:31
ከፈርዖን፤ እርሱ የኮራ ከወሰን አላፊዎቹ ነበርና፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
44:32
ከማወቅም ጋር በዓለማት ላይ በእርግጥ መረጥናቸው፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
44:33
ከታምራቶችም በውስጡ ግልጽ የኾነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው፡፡
ﯝﯞﯟﯠ
44:34
እነዚህ (የመካ ከሓዲዎች) በእርግጥ ይላሉ፡-
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
44:35
እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ አይደለችም፡፡ እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
44:36
እውነተኞችም እንደ ኾናችሁ አባቶቻችንን አምጡልን፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
44:37
እነርሱ በላጮች ናቸውን ወይስ የቱብበዕ ሕዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? አጠፋናቸው፡፡ እነርሱ አመጸኞች ነበሩና፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
44:38
ሰማያትንና ምድርንም በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ኾነን አልፈጠርንም፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎ
44:39
ሁለቱንም በምር እንጅ አልፈጠርናቸውም፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
44:40
የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው፡፡
ﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
44:41
ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይርረዱበት ቀን ነው፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
44:42
አላህ ያዘነለት ሰውና ያመነ ብቻ ሲቀር፡፡ (እርሱስ ይርረዳል)፡፡ እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነውና፡፡
ﭫﭬﭭﭮ
44:43
የዘቁመ ዛፍ
ﭯﭰﭱ
44:44
የኀጢኣተኛው ምግብ ነው፡፡
ﭲﭳﭴﭵﭶ
44:45
እንደ ዘይት አተላ ነው፡፡ በሆዶች ውስጥ የሚፈላ ሲኾን፡፡
ﭷﭸﭹ
44:46
እንደ ገነፈለ ውሃ አፈላል (የሚፈላ ሲኾን)፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
44:47
ያዙት፤ ወደ ገሀነም መካከልም በኀይል ጎትቱት፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
44:48
ከዚያም «ከራሱ በላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት፡፡»
ﮈﮉﮊﮋﮌﮍ
44:49
«ቅመስ፤ አንተ አሸናፊው ክብሩ ነህና» (ይባላል)፡፡
ﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
44:50
«ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
44:51
ጥንቁቆቹ በእርግጥ በጸጥተኛ መኖሪያ ውስጥ ናቸው፡፡
ﮛﮜﮝﮞ
44:52
በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
44:53
ፊት ለፊት የተቅጣጩ ኾነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩ
44:54
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፤ ዓይናማዎች የኾኑን ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
44:55
በእርሷም ውስጥ የተማመኑ ኾነው፤ ከፍራፍሬ ሁሉ ያዝዛሉ፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
44:56
የፊተኛይቱን ሞት እንጅ (ዳግመኛ) በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም፡፡ የገሀነምንም ቅጣት (አላህ) ጠበቃቸው፡፡
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
44:57
ከጌታህ በኾነ ችሮታ (ጠበቃቸው)፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
44:58
(ቁርኣኑን) በቋንቋህም ያገራነው (ሕዝቦችህ) ይገነዘቡ ዘንድ ብቻ ነው፡፡
ﯬﯭﯮﯯ
44:59
ተጠባበቅም እነርሱ ተጠባባቂዎች ናቸውና፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







