ሱረቱ አል-ሀቅቃ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አል-ሀቅቃ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ሀቅቃ ትርጉም. ሱረቱ አል-ሀቅቃ (Meccan) 52 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አል-ሀቅቃ

ﮯﮰ
69:1
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
ﮱﯓﯔ
69:2
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
ﯕﯖﯗﯘﯙ
69:3
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
ﯚﯛﯜﯝﯞ
69:4
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣ
69:5
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
69:6
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
69:7
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
ﯼﯽﯾﯿﰀﰁ
69:8
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
69:9
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
69:10
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
69:11
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
69:12
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
69:13
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻ
69:14
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
ﭼﭽﭾﭿ
69:15
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
69:16
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
ﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
69:17
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
69:18
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡ
69:19
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
69:20
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬ
69:21
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
ﮭﮮﮯﮰ
69:22
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
ﮱﯓﯔ
69:23
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
69:24
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨ
69:25
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
ﯩﯪﯫﯬﯭ
69:26
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
ﯮﯯﯰﯱ
69:27
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
69:28
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
ﯸﯹﯺﯻ
69:29
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
ﯼﯽﯾ
69:30
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
ﯿﰀﰁﰂ
69:31
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
69:32
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
ﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑ
69:33
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
ﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
69:34
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
ﰘﰙﰚﰛﰜﰝ
69:35
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
69:36
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
ﭗﭘﭙﭚﭛ
69:37
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
ﭜﭝﭞﭟﭠ
69:38
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
ﭡﭢﭣﭤ
69:39
በማታዩትም ነገር፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
69:40
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
69:41
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
69:42
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿ
69:43
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
69:44
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
ﮆﮇﮈﮉ
69:45
በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎ
69:46
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
69:47
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
ﮖﮗﮘﮙ
69:48
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟ
69:49
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
ﮠﮡﮢﮣﮤ
69:50
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
ﮥﮦﮧﮨ
69:51
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
69:52
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







