ሱረቱ አል-ዋቂዐ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ዋቂዐን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (96 አንቀጽ — مكية). አል-ዋቂዐ ስሙ, አል-ዋቂዐ ትርጉም, አል-ዋቂዐ mp3, አል-ዋቂዐ pdf.

ሱረቱ አል-ዋቂዐን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
إِذَا وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
خَافِضَةٌ رَّافِعَةٌ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
إِذَا رُجَّتِ الْأَرْضُ رَجًّا ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
وَبُسَّتِ الْجِبَالُ بَسًّا ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
فَكَانَتْ هَبَاءً مُّنبَثًّا ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
وَكُنتُمْ أَزْوَاجًا ثَلَاثَةً ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
فَأَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَأَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
وَالسَّابِقُونَ السَّابِقُونَ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
أُولَٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَقَلِيلٌ مِّنَ الْآخِرِينَ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
عَلَىٰ سُرُرٍ مَّوْضُونَةٍ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
مُّتَّكِئِينَ عَلَيْهَا مُتَقَابِلِينَ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
وَفَاكِهَةٍ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
وَلَحْمِ طَيْرٍ مِّمَّا يَشْتَهُونَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
وَحُورٌ عِينٌ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
كَأَمْثَالِ اللُّؤْلُؤِ الْمَكْنُونِ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا تَأْثِيمًا ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
إِلَّا قِيلًا سَلَامًا سَلَامًا ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
وَأَصْحَابُ الْيَمِينِ مَا أَصْحَابُ الْيَمِينِ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
فِي سِدْرٍ مَّخْضُودٍ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
وَطَلْحٍ مَّنضُودٍ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
وَظِلٍّ مَّمْدُودٍ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
وَمَاءٍ مَّسْكُوبٍ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
وَفَاكِهَةٍ كَثِيرَةٍ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
لَّا مَقْطُوعَةٍ وَلَا مَمْنُوعَةٍ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
وَفُرُشٍ مَّرْفُوعَةٍ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
إِنَّا أَنشَأْنَاهُنَّ إِنشَاءً ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
فَجَعَلْنَاهُنَّ أَبْكَارًا ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
عُرُبًا أَتْرَابًا ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
لِّأَصْحَابِ الْيَمِينِ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَثُلَّةٌ مِّنَ الْآخِرِينَ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَأَصْحَابُ الشِّمَالِ مَا أَصْحَابُ الشِّمَالِ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
فِي سَمُومٍ وَحَمِيمٍ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
وَظِلٍّ مِّن يَحْمُومٍ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
لَّا بَارِدٍ وَلَا كَرِيمٍ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا قَبْلَ ذَٰلِكَ مُتْرَفِينَ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
وَكَانُوا يَقُولُونَ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
قُلْ إِنَّ الْأَوَّلِينَ وَالْآخِرِينَ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
لَمَجْمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّكُمْ أَيُّهَا الضَّالُّونَ الْمُكَذِّبُونَ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
لَآكِلُونَ مِن شَجَرٍ مِّن زَقُّومٍ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
فَشَارِبُونَ عَلَيْهِ مِنَ الْحَمِيمِ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
فَشَارِبُونَ شُرْبَ الْهِيمِ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
هَٰذَا نُزُلُهُمْ يَوْمَ الدِّينِ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
نَحْنُ خَلَقْنَاكُمْ فَلَوْلَا تُصَدِّقُونَ ۝٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 57
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ ۝٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 58
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ ۝٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 59
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
نَحْنُ قَدَّرْنَا بَيْنَكُمُ الْمَوْتَ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ ۝٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 60
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ أَمْثَالَكُمْ وَنُنشِئَكُمْ فِي مَا لَا تَعْلَمُونَ ۝٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 61
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ النَّشْأَةَ الْأُولَىٰ فَلَوْلَا تَذَكَّرُونَ ۝٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 62
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
أَفَرَأَيْتُم مَّا تَحْرُثُونَ ۝٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 63
የምትዘሩትንም አያችሁን?
أَأَنتُمْ تَزْرَعُونَهُ أَمْ نَحْنُ الزَّارِعُونَ ۝٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 64
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
لَوْ نَشَاءُ لَجَعَلْنَاهُ حُطَامًا فَظَلْتُمْ تَفَكَّهُونَ ۝٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 65
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
إِنَّا لَمُغْرَمُونَ ۝٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 66
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ ۝٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 67
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
أَفَرَأَيْتُمُ الْمَاءَ الَّذِي تَشْرَبُونَ ۝٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 68
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
أَأَنتُمْ أَنزَلْتُمُوهُ مِنَ الْمُزْنِ أَمْ نَحْنُ الْمُنزِلُونَ ۝٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 69
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
لَوْ نَشَاءُ جَعَلْنَاهُ أُجَاجًا فَلَوْلَا تَشْكُرُونَ ۝٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 70
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
أَفَرَأَيْتُمُ النَّارَ الَّتِي تُورُونَ ۝٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 71
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
أَأَنتُمْ أَنشَأْتُمْ شَجَرَتَهَا أَمْ نَحْنُ الْمُنشِئُونَ ۝٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 72
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
نَحْنُ جَعَلْنَاهَا تَذْكِرَةً وَمَتَاعًا لِّلْمُقْوِينَ ۝٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 73
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ ۝٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 74
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
۞ فَلَا أُقْسِمُ بِمَوَاقِعِ النُّجُومِ ۝٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 75
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
وَإِنَّهُ لَقَسَمٌ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ ۝٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 76
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
إِنَّهُ لَقُرْآنٌ كَرِيمٌ ۝٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 77
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
فِي كِتَابٍ مَّكْنُونٍ ۝٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 78
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
لَّا يَمَسُّهُ إِلَّا الْمُطَهَّرُونَ ۝٧٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 79
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ ۝٨٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 80
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
أَفَبِهَٰذَا الْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ ۝٨١
📖 ትርጉም አንቀጽ 81
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ ۝٨٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 82
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
فَلَوْلَا إِذَا بَلَغَتِ الْحُلْقُومَ ۝٨٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 83
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
وَأَنتُمْ حِينَئِذٍ تَنظُرُونَ ۝٨٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 84
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنكُمْ وَلَٰكِن لَّا تُبْصِرُونَ ۝٨٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 85
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
فَلَوْلَا إِن كُنتُمْ غَيْرَ مَدِينِينَ ۝٨٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 86
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
تَرْجِعُونَهَا إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ ۝٨٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 87
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
فَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُقَرَّبِينَ ۝٨٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 88
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
فَرَوْحٌ وَرَيْحَانٌ وَجَنَّتُ نَعِيمٍ ۝٨٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 89
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
وَأَمَّا إِن كَانَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ ۝٩٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 90
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
فَسَلَامٌ لَّكَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ ۝٩١
📖 ትርጉም አንቀጽ 91
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
وَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُكَذِّبِينَ الضَّالِّينَ ۝٩٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 92
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
فَنُزُلٌ مِّنْ حَمِيمٍ ۝٩٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 93
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
وَتَصْلِيَةُ جَحِيمٍ ۝٩٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 94
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ الْيَقِينِ ۝٩٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 95
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ ۝٩٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 96
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
← 55 አል-ዋቂዐ (56/114) 57 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ዋቂዐ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

56الواقعة Al-Waqi'ah 📚 96 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ዋቂዐ — 96 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers