ሱረቱ ኑህ
PDF —
Built right in your browser — download starts automatically
ሱረቱ ኑህ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ ኑህ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ ኑህ ትርጉም. ኑህ (Meccan) 28 አንቀጽ.
Related
- ኑህ ትርጉምአማርኛ
- ኑህ mp3ስሙ
- Quran Index አማርኛ114
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ ኑህ

ﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
እኛ ኑሕን «ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ በማለት ወደ ሕዝቦቹ ላክነው፡፡»
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍ
(እርሱም) አለ «ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ለእናንተ ገላጭ የኾንኩ አስጠንቃቂ ነኝ፡፡
ﮎﮏﮐﮑﮒﮓ
«አላህን ተገዙት፣ ፍሩትም፣ ታዘዙኝም በማለት፤ (አስጠንቃቂ ነኝ)፡፡
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨ
«ለእናንተ ከኀጢኣቶቻችሁ ይምራልና፡፡ ወደተወሰነው ጊዜም ያቆያችኋል፡፡ የአላህ (የወሰነው) ጊዜ በመጣ ወቅት አይቆይም፡፡ የምታውቁት ብትኾኑ ኖሮ (በታዘዛችሁ ነበር)፡፡»
ﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰ
(ስለ ተቃወሙትም) «አለ ጌታዬ ሆይ! እኔ ሌሊትም ቀንም ሕዝቦቼን ጠራሁ፡፡
ﮱﯓﯔﯕﯖﯗ
«ጥሪየም መሸሽን እንጅ ሌላ አልጨመረላቸውም፡፡
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
«እኔም ለእነርሱ ትምር ዘንድ (ወደ እምነት) በጠራኋቸው ቁጥር ጣቶቻቸውን በጆሮዎቻቸው ውስጥ አደረጉ፡፡ ልብሶቻቸውንም ተከናነቡ፡፡ (በመጥፎ ሥራቸው ላይ) ዘወተሩም፡፡ (ያለ ልክ) መኩራትንም ኮሩ፡፡
ﯧﯨﯩﯪﯫ
«ከዚያም እኔ በጩኸት ጠራኋቸው፡፡
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
«ከዚያም እኔ ለእነርሱ ገለጽኩ፡፡ ለእነርሱም መመስጠርን መሰጠርኩ
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
«አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
«በእናንተ ላይ ዝናምን ተከታታይ አድርጎ ይልካል፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟ
«በገንዘቦችና በልጆችም ይለግሰላችኋል፡፡ ለእናንተም አትክልቶችን ያደርግላችኋል፡፡ ለእናንተም ወንዞችን ያደርግላችኋል፡፡»
ﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
ለአላህ ልቅናን የማትሹት ለእናንተ ምን አላችሁ?
ﭧﭨﭩﭪ
በልዩ ልዩ ኹኔታዎች በእርግጥ የፈጠራችሁ ሲኾን፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
አላህ ሰባትን ሰማያት አንዱ ካንዱ በላይ ሲኾን እንዴት እንደፈጠረ አታዩምን?
ﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻ
በውስጣቸውም ጨረቃን አብሪ አደረገ፡፡ ፀሐይንም ብርሃን አደረገ፡፡
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
አላህም ከምድር ማብቀልን አበቀላችሁ፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
ከዚያም በውስጧ ይመልሳችኋል፡፡ ማውጣትንም ያወጣችኋል፡፡
ﮈﮉﮊﮋﮌﮍ
አላህም ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ አደረጋት፡፡
ﮎﮏﮐﮑﮒ
ከእርሷ ሰፋፊዎችን መንገዶች ትገቡ ዘንድ፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
ኑሕ አለ፡- «ጌታዬ ሆይ! እነሱ አምመጹብኝ፡፡ ገንዘቡና ልጁም ከጥፋት በስተቀር ያልጨመረለትን ሰው ተከተሉ፡፡
ﮡﮢﮣﮤ
«ታላቅንም ተንኮል የመከሩትን ሰዎች» (ተከተሉ)፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
አሉም «አምላኮቻችሁን አትተዉ፡፡ ወድንም፣ ሱዋዕንም፣ የጉሥንም፣ የዑቅንም ነስርንም አትተው፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
«በእርግጥም ብዙዎችን አሳሳቱ፡፡ ከሓዲዎችንም ጥመትን እንጅ ሌላን አትጨምርላቸው» (አለ)፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
በኀጢኣቶቻቸው ምክንያት ተሰጠሙ፡፡ እሳትንም እንዲገቡ ተደረጉ፡፡ ለእነርሱም ከአላህ ሌላ የኾኑ ረዳቶችን አላገኙም፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
ኑሕም አለ «ጌታዬ ሆይ! ከከሓዲዎቹ በምድር ላይ አንድንም አትተው፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
«አንተ ብትተዋቸው ባሮችህን ያሳስታሉና፡፡ ኀጢኣተኛ ከሓዲንም እንጅ ሌላን አይወልዱም፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑ
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ምእመን ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው፤» (አለ)፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Tuesday, August 18, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







