PDF —
44 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ አል-መዓሪጅ pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ አል-መዓሪጅ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-መዓሪጅ ትርጉም. ሱረቱ አል-መዓሪጅ (Meccan) 44 አንቀጽ.

← አል-ሀቅቃሱረቱ አል-መዓሪጅ ኑህ →


44 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﮮﮯﮰﮱﯓ
70:1 ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘ
70:2 በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝ
70:3 የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
70:4 መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
ﯪﯫﯬﯭ
70:5 መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
ﯮﯯﯰﯱ
70:6 እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
ﯲﯳﯴ
70:7 እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
70:8 ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
ﯺﯻﯼﯽ
70:9 ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂ
70:10 ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
70:11 (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
ﭜﭝﭞ
70:12 በሚስቱም በወንድሙም፡፡
ﭟﭠﭡﭢ
70:13 በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
70:14 በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮ
70:15 ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
ﭯﭰﭱ
70:16 የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
ﭲﭳﭴﭵﭶ
70:17 (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
ﭷﭸﭹ
70:18 ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
70:19 ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄ
70:20 ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
ﮅﮆﮇﮈﮉ
70:21 መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
ﮊﮋﮌ
70:22 ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
70:23 እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
70:24 እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
ﮙﮚﮛ
70:25 ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠ
70:26 እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
70:27 እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
70:28 የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓ
70:29 እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
70:30 በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
70:31 ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
70:32 እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱ
70:33 እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
70:34 እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼ
70:35 እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
ﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
70:36 ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈ
70:37 ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
ﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑ
70:38 ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
ﰒﰓﰔﰕﰖﰗﰘ
70:39 ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
ﰙﰚﰛﰜﰝﰞﰟﰠ
70:40 በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙ
70:41 ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
70:42 ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
70:43 ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷ
70:44 ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Wednesday, September 9, 2026

Don't forget us in your sincere prayers