ሱረቱ አል-ሙጦፊፊን ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ሙጦፊፊንን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (36 አንቀጽ — مكية). አል-ሙጦፊፊን ስሙ, አል-ሙጦፊፊን ትርጉም, አል-ሙጦፊፊን mp3, አል-ሙጦፊፊን pdf.

ሱረቱ አል-ሙጦፊፊንን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
الَّذِينَ إِذَا اكْتَالُوا عَلَى النَّاسِ يَسْتَوْفُونَ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
أَلَا يَظُنُّ أُولَٰئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
لِيَوْمٍ عَظِيمٍ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
በታላቁ ቀን፡፡
يَوْمَ يَقُومُ النَّاسُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٍ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا سِجِّينٌ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
كِتَابٌ مَّرْقُومٌ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
الَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
وَمَا يُكَذِّبُ بِهِ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا يَكْسِبُونَ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
كَلَّا إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّمَحْجُوبُونَ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُو الْجَحِيمِ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْأَبْرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا عِلِّيُّونَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
كِتَابٌ مَّرْقُومٌ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
تَعْرِفُ فِي وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ النَّعِيمِ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍ مَّخْتُومٍ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
خِتَامُهُ مِسْكٌ ۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
وَمِزَاجُهُ مِن تَسْنِيمٍ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
إِنَّ الَّذِينَ أَجْرَمُوا كَانُوا مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا يَضْحَكُونَ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
وَإِذَا مَرُّوا بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
وَإِذَا انقَلَبُوا إِلَىٰ أَهْلِهِمُ انقَلَبُوا فَكِهِينَ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوا إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَضَالُّونَ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
وَمَا أُرْسِلُوا عَلَيْهِمْ حَافِظِينَ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
فَالْيَوْمَ الَّذِينَ آمَنُوا مِنَ الْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
هَلْ ثُوِّبَ الْكُفَّارُ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
← 82 አል-ሙጦፊፊን (83/114) 84 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ሙጦፊፊን አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

83المطففين Al-Mutaffifin 📚 36 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ሙጦፊፊን — 36 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers