Surah Al-Mursalat with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Mursalat | المرسلات - Ayat Count 50 - The number of the surah in moshaf: 77 - The meaning of the surah in English: Those Sent Forth.

وَالْمُرْسَلَاتِ عُرْفًا(1)

 ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

فَالْعَاصِفَاتِ عَصْفًا(2)

 በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

وَالنَّاشِرَاتِ نَشْرًا(3)

 መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

فَالْفَارِقَاتِ فَرْقًا(4)

 መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

فَالْمُلْقِيَاتِ ذِكْرًا(5)

 መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

عُذْرًا أَوْ نُذْرًا(6)

 ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَاقِعٌ(7)

 ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

فَإِذَا النُّجُومُ طُمِسَتْ(8)

 ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

وَإِذَا السَّمَاءُ فُرِجَتْ(9)

 ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

وَإِذَا الْجِبَالُ نُسِفَتْ(10)

 ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

وَإِذَا الرُّسُلُ أُقِّتَتْ(11)

 መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

لِأَيِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ(12)

 ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

لِيَوْمِ الْفَصْلِ(13)

 ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الْفَصْلِ(14)

 የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(15)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نُهْلِكِ الْأَوَّلِينَ(16)

 የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ الْآخِرِينَ(17)

 ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ(18)

 በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(19)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَخْلُقكُّم مِّن مَّاءٍ مَّهِينٍ(20)

 ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

فَجَعَلْنَاهُ فِي قَرَارٍ مَّكِينٍ(21)

 በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

إِلَىٰ قَدَرٍ مَّعْلُومٍ(22)

 እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም

فَقَدَرْنَا فَنِعْمَ الْقَادِرُونَ(23)

 መጣኞች ነን!

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(24)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ كِفَاتًا(25)

 ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

أَحْيَاءً وَأَمْوَاتًا(26)

 ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

وَجَعَلْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ شَامِخَاتٍ وَأَسْقَيْنَاكُم مَّاءً فُرَاتًا(27)

 በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(28)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

انطَلِقُوا إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ(29)

 «ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

انطَلِقُوا إِلَىٰ ظِلٍّ ذِي ثَلَاثِ شُعَبٍ(30)

 «ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

لَّا ظَلِيلٍ وَلَا يُغْنِي مِنَ اللَّهَبِ(31)

 አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

إِنَّهَا تَرْمِي بِشَرَرٍ كَالْقَصْرِ(32)

 እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

كَأَنَّهُ جِمَالَتٌ صُفْرٌ(33)

 (ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(34)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ لَا يَنطِقُونَ(35)

 ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

وَلَا يُؤْذَنُ لَهُمْ فَيَعْتَذِرُونَ(36)

 ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(37)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ ۖ جَمَعْنَاكُمْ وَالْأَوَّلِينَ(38)

 ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

فَإِن كَانَ لَكُمْ كَيْدٌ فَكِيدُونِ(39)

 ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(40)

 ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي ظِلَالٍ وَعُيُونٍ(41)

 ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

وَفَوَاكِهَ مِمَّا يَشْتَهُونَ(42)

 ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ(43)

 «ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(44)

 እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(45)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

كُلُوا وَتَمَتَّعُوا قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجْرِمُونَ(46)

 ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(47)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ارْكَعُوا لَا يَرْكَعُونَ(48)

 «ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ(49)

 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

فَبِأَيِّ حَدِيثٍ بَعْدَهُ يُؤْمِنُونَ(50)

 ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah Al-Mursalat with the voice of the most famous Quran reciters :

surah Al-Mursalat mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter Al-Mursalat Complete with high quality
surah Al-Mursalat Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah Al-Mursalat Bandar Balila
Bandar Balila
surah Al-Mursalat Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah Al-Mursalat Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah Al-Mursalat Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah Al-Mursalat Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah Al-Mursalat Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah Al-Mursalat Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah Al-Mursalat Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah Al-Mursalat Fares Abbad
Fares Abbad
surah Al-Mursalat Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah Al-Mursalat Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah Al-Mursalat Al Hosary
Al Hosary
surah Al-Mursalat Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah Al-Mursalat Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب