سورة المعارج بالأمهرية

  1. استمع للسورة
  2. سور أخرى
  3. ترجمة السورة
القرآن الكريم | ترجمة معاني القرآن | اللغة الأمهرية | سورة المعارج | Maarij - عدد آياتها 44 - رقم السورة في المصحف: 70 - معنى السورة بالإنجليزية: The Ways of Ascent.

سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ(1)

ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡

لِّلْكَافِرِينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ(2)

በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡

مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ(3)

የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ(4)

መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡

فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا(5)

መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡

إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا(6)

እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡

وَنَرَاهُ قَرِيبًا(7)

እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡

يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ(8)

ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡

وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ(9)

ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡

وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا(10)

ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ(11)

(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡

وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ(12)

በሚስቱም በወንድሙም፡፡

وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ(13)

በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡

وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ(14)

በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ(15)

ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡

نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ(16)

የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡

تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ(17)

(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡

وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰ(18)

ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡

۞ إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا(19)

ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡

إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا(20)

ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡

وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا(21)

መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡

إِلَّا الْمُصَلِّينَ(22)

ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡

الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ(23)

እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ(24)

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡

لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ(25)

ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡

وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ(26)

እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡

وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ(27)

እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡

إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ(28)

የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ(29)

እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ(30)

በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡

فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ(31)

ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ(32)

እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ(33)

እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ(34)

እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡

أُولَٰئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ(35)

እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡

فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ(36)

ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ(37)

ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡

أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ(38)

ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

كَلَّا ۖ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ(39)

ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ(40)

በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ(41)

ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّىٰ يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ(42)

ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍ يُوفِضُونَ(43)

ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۚ ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ(44)

ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡


المزيد من السور باللغة الأمهرية:

سورة البقرة آل عمران سورة النساء
سورة المائدة سورة يوسف سورة ابراهيم
سورة الحجر سورة الكهف سورة مريم
سورة السجدة سورة يس سورة الدخان
سورة النجم سورة الرحمن سورة الواقعة
سورة الحشر سورة الملك سورة الحاقة

تحميل سورة المعارج بصوت أشهر القراء :

قم باختيار القارئ للاستماع و تحميل سورة المعارج كاملة بجودة عالية
سورة المعارج أحمد العجمي
أحمد العجمي
سورة المعارج خالد الجليل
خالد الجليل
سورة المعارج سعد الغامدي
سعد الغامدي
سورة المعارج سعود الشريم
سعود الشريم
سورة المعارج عبد الباسط عبد الصمد
عبد الباسط
سورة المعارج عبد الله عواد الجهني
عبد الله الجهني
سورة المعارج علي الحذيفي
علي الحذيفي
سورة المعارج فارس عباد
فارس عباد
سورة المعارج ماهر المعيقلي
ماهر المعيقلي
سورة المعارج محمد جبريل
محمد جبريل
سورة المعارج محمد صديق المنشاوي
المنشاوي
سورة المعارج الحصري
الحصري
سورة المعارج العفاسي
مشاري العفاسي
سورة المعارج ناصر القطامي
ناصر القطامي
سورة المعارج ياسر الدوسري
ياسر الدوسري



Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب