ሱረቱ አን-ናዚዓት ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አን-ናዚዓትን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (46 አንቀጽ — مكية). አን-ናዚዓት ስሙ, አን-ናዚዓት ትርጉም, አን-ናዚዓት mp3, አን-ናዚዓት pdf.

ሱረቱ አን-ናዚዓትን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
وَالسَّابِحَاتِ سَبْحًا ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
فَالسَّابِقَاتِ سَبْقًا ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
فَالْمُدَبِّرَاتِ أَمْرًا ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
يَوْمَ تَرْجُفُ الرَّاجِفَةُ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
تَتْبَعُهَا الرَّادِفَةُ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
قُلُوبٌ يَوْمَئِذٍ وَاجِفَةٌ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
أَبْصَارُهَا خَاشِعَةٌ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
يَقُولُونَ أَإِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِي الْحَافِرَةِ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا نَّخِرَةً ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
قَالُوا تِلْكَ إِذًا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
فَإِذَا هُم بِالسَّاهِرَةِ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
إِذْ نَادَاهُ رَبُّهُ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰ أَن تَزَكَّىٰ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
فَأَرَاهُ الْآيَةَ الْكُبْرَىٰ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
فَأَخَذَهُ اللَّهُ نَكَالَ الْآخِرَةِ وَالْأُولَىٰ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبْرَةً لِّمَن يَخْشَىٰ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
أَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاءُ ۚ بَنَاهَا ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّاهَا ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَاهَا ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَاهَا ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءَهَا وَمَرْعَاهَا ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
وَالْجِبَالَ أَرْسَاهَا ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
مَتَاعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
فَإِذَا جَاءَتِ الطَّامَّةُ الْكُبْرَىٰ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
يَوْمَ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ مَا سَعَىٰ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
የካደ ሰውማ፣
وَآثَرَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
فَإِنَّ الْجَحِيمَ هِيَ الْمَأْوَىٰ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَىٰ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَىٰ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
يَسْأَلُونَكَ عَنِ السَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَاهَا ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَاهَا ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَاهَا ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
إِنَّمَا أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَاهَا ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوا إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَاهَا ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
← 78 አን-ናዚዓት (79/114) 80 →
ማንበብ ሱረቱ አን-ናዚዓት አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

79النازعات An-Nazi'at 📚 46 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አን-ናዚዓት — 46 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers