ሱረቱ አን-ነበእ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አን-ነበእ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አን-ነበእ ትርጉም. ሱረቱ አን-ነበእ (Meccan) 40 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አን-ነበእ

ﭑﭒﭓ
78:1
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
ﭔﭕﭖﭗ
78:2
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜ
78:3
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
ﭝﭞﭟ
78:4
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ﭠﭡﭢﭣ
78:5
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨ
78:6
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
ﭩﭪﭫ
78:7
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
ﭬﭭﭮ
78:8
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
ﭯﭰﭱﭲ
78:9
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
ﭳﭴﭵﭶ
78:10
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
ﭷﭸﭹﭺ
78:11
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿ
78:12
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
ﮀﮁﮂﮃ
78:13
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
78:14
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎ
78:15
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
ﮏﮐﮑ
78:16
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
78:17
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
78:18
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣ
78:19
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨ
78:20
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
78:21
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
ﮮﮯﮰ
78:22
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
ﮱﯓﯔﯕ
78:23
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
78:24
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
ﯝﯞﯟﯠ
78:25
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
ﯡﯢﯣ
78:26
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
78:27
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
ﯪﯫﯬﯭ
78:28
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
ﯮﯯﯰﯱﯲ
78:29
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
ﯳﯴﯵﯶﯷﯸ
78:30
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
ﭑﭒﭓﭔ
78:31
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
ﭕﭖﭗ
78:32
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
ﭘﭙﭚ
78:33
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
ﭛﭜﭝ
78:34
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
78:35
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
78:36
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
78:37
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
78:38
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
78:39
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡ
78:40
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







