ሱረቱ አል-ሙርሳላት ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ሙርሳላትን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (50 አንቀጽ — مكية). አል-ሙርሳላት ስሙ, አል-ሙርሳላት ትርጉም, አል-ሙርሳላት mp3, አል-ሙርሳላት pdf.

ሱረቱ አል-ሙርሳላትን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَالْمُرْسَلَاتِ عُرْفًا ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
فَالْعَاصِفَاتِ عَصْفًا ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
وَالنَّاشِرَاتِ نَشْرًا ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
فَالْفَارِقَاتِ فَرْقًا ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
فَالْمُلْقِيَاتِ ذِكْرًا ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
عُذْرًا أَوْ نُذْرًا ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَاقِعٌ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
فَإِذَا النُّجُومُ طُمِسَتْ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
وَإِذَا السَّمَاءُ فُرِجَتْ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
وَإِذَا الْجِبَالُ نُسِفَتْ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
وَإِذَا الرُّسُلُ أُقِّتَتْ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
لِأَيِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
لِيَوْمِ الْفَصْلِ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا يَوْمُ الْفَصْلِ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
أَلَمْ نُهْلِكِ الْأَوَّلِينَ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ الْآخِرِينَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
أَلَمْ نَخْلُقكُّم مِّن مَّاءٍ مَّهِينٍ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
فَجَعَلْنَاهُ فِي قَرَارٍ مَّكِينٍ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
إِلَىٰ قَدَرٍ مَّعْلُومٍ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
فَقَدَرْنَا فَنِعْمَ الْقَادِرُونَ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
መጣኞች ነን!
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
أَلَمْ نَجْعَلِ الْأَرْضَ كِفَاتًا ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
أَحْيَاءً وَأَمْوَاتًا ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
وَجَعَلْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ شَامِخَاتٍ وَأَسْقَيْنَاكُم مَّاءً فُرَاتًا ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
انطَلِقُوا إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
انطَلِقُوا إِلَىٰ ظِلٍّ ذِي ثَلَاثِ شُعَبٍ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
لَّا ظَلِيلٍ وَلَا يُغْنِي مِنَ اللَّهَبِ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
إِنَّهَا تَرْمِي بِشَرَرٍ كَالْقَصْرِ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
كَأَنَّهُ جِمَالَتٌ صُفْرٌ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
هَٰذَا يَوْمُ لَا يَنطِقُونَ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
وَلَا يُؤْذَنُ لَهُمْ فَيَعْتَذِرُونَ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ ۖ جَمَعْنَاكُمْ وَالْأَوَّلِينَ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
فَإِن كَانَ لَكُمْ كَيْدٌ فَكِيدُونِ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي ظِلَالٍ وَعُيُونٍ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
وَفَوَاكِهَ مِمَّا يَشْتَهُونَ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
كُلُوا وَتَمَتَّعُوا قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجْرِمُونَ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ارْكَعُوا لَا يَرْكَعُونَ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
فَبِأَيِّ حَدِيثٍ بَعْدَهُ يُؤْمِنُونَ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
← 76 አል-ሙርሳላት (77/114) 78 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ሙርሳላት አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

77المرسلات Al-Mursalat 📚 50 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ሙርሳላት — 50 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers