Surah Al-Maarij with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Maarij | المعارج - Ayat Count 44 - The number of the surah in moshaf: 70 - The meaning of the surah in English: The Ways of Ascent.

سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ(1)

 ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡

لِّلْكَافِرِينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ(2)

 በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡

مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ(3)

 የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ(4)

 መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡

فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا(5)

 መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡

إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا(6)

 እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡

وَنَرَاهُ قَرِيبًا(7)

 እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡

يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ(8)

 ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡

وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ(9)

 ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡

وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا(10)

 ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ(11)

 (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡

وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ(12)

 በሚስቱም በወንድሙም፡፡

وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ(13)

 በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡

وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ(14)

 በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ(15)

 ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡

نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ(16)

 የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡

تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ(17)

 (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡

وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰ(18)

 ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡

۞ إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا(19)

 ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡

إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا(20)

 ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡

وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا(21)

 መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡

إِلَّا الْمُصَلِّينَ(22)

 ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡

الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ(23)

 እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ(24)

 እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡

لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ(25)

 ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡

وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ(26)

 እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡

وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ(27)

 እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡

إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ(28)

 የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ(29)

 እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ(30)

 በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡

فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ(31)

 ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ(32)

 እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ(33)

 እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ(34)

 እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡

أُولَٰئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ(35)

 እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡

فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ(36)

 ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ(37)

 ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡

أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ(38)

 ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

كَلَّا ۖ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ(39)

 ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ(40)

 በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ(41)

 ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّىٰ يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ(42)

 ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍ يُوفِضُونَ(43)

 ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۚ ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ(44)

 ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah Al-Maarij with the voice of the most famous Quran reciters :

surah Al-Maarij mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter Al-Maarij Complete with high quality
surah Al-Maarij Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah Al-Maarij Bandar Balila
Bandar Balila
surah Al-Maarij Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah Al-Maarij Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah Al-Maarij Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah Al-Maarij Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah Al-Maarij Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah Al-Maarij Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah Al-Maarij Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah Al-Maarij Fares Abbad
Fares Abbad
surah Al-Maarij Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah Al-Maarij Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah Al-Maarij Al Hosary
Al Hosary
surah Al-Maarij Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah Al-Maarij Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب