ሱረቱ ዐበሰ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ ዐበሰን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (42 አንቀጽ — مكية). ዐበሰ ስሙ, ዐበሰ ትርጉም, ዐበሰ mp3, ዐበሰ pdf.

ሱረቱ ዐበሰን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
عَبَسَ وَتَوَلَّىٰ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
أَن جَاءَهُ الْأَعْمَىٰ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُ يَزَّكَّىٰ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ الذِّكْرَىٰ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
أَمَّا مَنِ اسْتَغْنَىٰ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
የተብቃቃው ሰውማ፤
فَأَنتَ لَهُ تَصَدَّىٰ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
وَمَا عَلَيْكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
وَأَمَّا مَن جَاءَكَ يَسْعَىٰ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
وَهُوَ يَخْشَىٰ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
فَأَنتَ عَنْهُ تَلَهَّىٰ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
كَلَّا إِنَّهَا تَذْكِرَةٌ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
فَمَن شَاءَ ذَكَرَهُ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
فِي صُحُفٍ مُّكَرَّمَةٍ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
مَّرْفُوعَةٍ مُّطَهَّرَةٍ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
بِأَيْدِي سَفَرَةٍ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
كِرَامٍ بَرَرَةٍ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
قُتِلَ الْإِنسَانُ مَا أَكْفَرَهُ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
مِنْ أَيِّ شَيْءٍ خَلَقَهُ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
مِن نُّطْفَةٍ خَلَقَهُ فَقَدَّرَهُ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ثُمَّ السَّبِيلَ يَسَّرَهُ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ثُمَّ أَمَاتَهُ فَأَقْبَرَهُ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ثُمَّ إِذَا شَاءَ أَنشَرَهُ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
كَلَّا لَمَّا يَقْضِ مَا أَمَرَهُ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
فَلْيَنظُرِ الْإِنسَانُ إِلَىٰ طَعَامِهِ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
أَنَّا صَبَبْنَا الْمَاءَ صَبًّا ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ثُمَّ شَقَقْنَا الْأَرْضَ شَقًّا ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
فَأَنبَتْنَا فِيهَا حَبًّا ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
وَعِنَبًا وَقَضْبًا ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
وَزَيْتُونًا وَنَخْلًا ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
وَحَدَائِقَ غُلْبًا ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
وَفَاكِهَةً وَأَبًّا ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
مَّتَاعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
فَإِذَا جَاءَتِ الصَّاخَّةُ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
يَوْمَ يَفِرُّ الْمَرْءُ مِنْ أَخِيهِ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
وَأُمِّهِ وَأَبِيهِ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
ከናቱም ካባቱም፤
وَصَاحِبَتِهِ وَبَنِيهِ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ከሚስቱም ከልጁም፤
لِكُلِّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ يَوْمَئِذٍ شَأْنٌ يُغْنِيهِ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ مُّسْفِرَةٌ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ضَاحِكَةٌ مُّسْتَبْشِرَةٌ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ عَلَيْهَا غَبَرَةٌ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
تَرْهَقُهَا قَتَرَةٌ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
أُولَٰئِكَ هُمُ الْكَفَرَةُ الْفَجَرَةُ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
← 79 ዐበሰ (80/114) 81 →
ማንበብ ሱረቱ ዐበሰ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

80عبس 'Abasa 📚 42 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ ዐበሰ — 42 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers