ሱረቱ ዐበሰ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ ዐበሰ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ ዐበሰ ትርጉም. ሱረቱ ዐበሰ (Meccan) 42 አንቀጽ.
Related
- ሱረቱ ዐበሰ ትርጉምአማርኛ
- ሱረቱ ዐበሰ mp3ስሙ
- Quran Index አማርኛ114
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ ዐበሰ

ﭑﭒﭓ
80:1
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
ﭔﭕﭖﭗ
80:2
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜ
80:3
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
ﭝﭞﭟﭠﭡ
80:4
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
ﭢﭣﭤﭥ
80:5
የተብቃቃው ሰውማ፤
ﭦﭧﭨﭩ
80:6
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮ
80:7
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳ
80:8
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
ﭴﭵﭶ
80:9
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
ﭷﭸﭹﭺ
80:10
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
ﭻﭼﭽﭾ
80:11
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
ﭿﮀﮁﮂ
80:12
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
ﮃﮄﮅﮆ
80:13
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
ﮇﮈﮉ
80:14
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
ﮊﮋﮌ
80:15
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
ﮍﮎﮏ
80:16
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔ
80:17
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
ﮕﮖﮗﮘﮙ
80:18
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
ﮚﮛﮜﮝﮞ
80:19
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ﮟﮠﮡﮢ
80:20
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ﮣﮤﮥﮦ
80:21
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫ
80:22
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
80:23
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
ﯓﯔﯕﯖﯗ
80:24
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
ﯘﯙﯚﯛﯜ
80:25
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ﯝﯞﯟﯠﯡ
80:26
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
ﯢﯣﯤﯥ
80:27
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
ﯦﯧﯨ
80:28
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
ﯩﯪﯫ
80:29
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
ﯬﯭﯮ
80:30
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
ﯯﯰﯱ
80:31
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
ﯲﯳﯴﯵ
80:32
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
ﯶﯷﯸﯹ
80:33
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿ
80:34
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
ﰀﰁﰂ
80:35
ከናቱም ካባቱም፤
ﰃﰄﰅ
80:36
ከሚስቱም ከልጁም፤
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
80:37
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
ﰍﰎﰏﰐ
80:38
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ﰑﰒﰓ
80:39
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
ﰔﰕﰖﰗﰘ
80:40
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
ﭑﭒﭓ
80:41
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
ﭔﭕﭖﭗﭘ
80:42
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







