ሱረቱ አል-ሀቅቃ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ሀቅቃን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (52 አንቀጽ — مكية). አል-ሀቅቃ ስሙ, አል-ሀቅቃ ትርጉም, አል-ሀቅቃ mp3, አል-ሀቅቃ pdf.

ሱረቱ አል-ሀቅቃን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
الْحَاقَّةُ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
مَا الْحَاقَّةُ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
وَمَا أَدْرَاكَ مَا الْحَاقَّةُ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
كَذَّبَتْ ثَمُودُ وَعَادٌ بِالْقَارِعَةِ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهْلِكُوا بِالطَّاغِيَةِ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
وَأَمَّا عَادٌ فَأُهْلِكُوا بِرِيحٍ صَرْصَرٍ عَاتِيَةٍ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
سَخَّرَهَا عَلَيْهِمْ سَبْعَ لَيَالٍ وَثَمَانِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومًا فَتَرَى الْقَوْمَ فِيهَا صَرْعَىٰ كَأَنَّهُمْ أَعْجَازُ نَخْلٍ خَاوِيَةٍ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
فَهَلْ تَرَىٰ لَهُم مِّن بَاقِيَةٍ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
وَجَاءَ فِرْعَوْنُ وَمَن قَبْلَهُ وَالْمُؤْتَفِكَاتُ بِالْخَاطِئَةِ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
فَعَصَوْا رَسُولَ رَبِّهِمْ فَأَخَذَهُمْ أَخْذَةً رَّابِيَةً ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
إِنَّا لَمَّا طَغَى الْمَاءُ حَمَلْنَاكُمْ فِي الْجَارِيَةِ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
لِنَجْعَلَهَا لَكُمْ تَذْكِرَةً وَتَعِيَهَا أُذُنٌ وَاعِيَةٌ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
فَإِذَا نُفِخَ فِي الصُّورِ نَفْخَةٌ وَاحِدَةٌ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
وَحُمِلَتِ الْأَرْضُ وَالْجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةً وَاحِدَةً ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
فَيَوْمَئِذٍ وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
وَانشَقَّتِ السَّمَاءُ فَهِيَ يَوْمَئِذٍ وَاهِيَةٌ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
وَالْمَلَكُ عَلَىٰ أَرْجَائِهَا ۚ وَيَحْمِلُ عَرْشَ رَبِّكَ فَوْقَهُمْ يَوْمَئِذٍ ثَمَانِيَةٌ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
يَوْمَئِذٍ تُعْرَضُونَ لَا تَخْفَىٰ مِنكُمْ خَافِيَةٌ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
فَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ فَيَقُولُ هَاؤُمُ اقْرَءُوا كِتَابِيَهْ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَاقٍ حِسَابِيَهْ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
فَهُوَ فِي عِيشَةٍ رَّاضِيَةٍ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٍ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
قُطُوفُهَا دَانِيَةٌ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا أَسْلَفْتُمْ فِي الْأَيَّامِ الْخَالِيَةِ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِشِمَالِهِ فَيَقُولُ يَا لَيْتَنِي لَمْ أُوتَ كِتَابِيَهْ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
وَلَمْ أَدْرِ مَا حِسَابِيَهْ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
يَا لَيْتَهَا كَانَتِ الْقَاضِيَةَ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
مَا أَغْنَىٰ عَنِّي مَالِيَهْ ۜ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
هَلَكَ عَنِّي سُلْطَانِيَهْ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
خُذُوهُ فَغُلُّوهُ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
ثُمَّ الْجَحِيمَ صَلُّوهُ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
ثُمَّ فِي سِلْسِلَةٍ ذَرْعُهَا سَبْعُونَ ذِرَاعًا فَاسْلُكُوهُ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
إِنَّهُ كَانَ لَا يُؤْمِنُ بِاللَّهِ الْعَظِيمِ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ الْمِسْكِينِ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
فَلَيْسَ لَهُ الْيَوْمَ هَاهُنَا حَمِيمٌ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنْ غِسْلِينٍ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
لَّا يَأْكُلُهُ إِلَّا الْخَاطِئُونَ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
فَلَا أُقْسِمُ بِمَا تُبْصِرُونَ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
وَمَا لَا تُبْصِرُونَ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
በማታዩትም ነገር፡፡
إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَاعِرٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تُؤْمِنُونَ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
وَلَا بِقَوْلِ كَاهِنٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تَذَكَّرُونَ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
وَلَوْ تَقَوَّلَ عَلَيْنَا بَعْضَ الْأَقَاوِيلِ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
لَأَخَذْنَا مِنْهُ بِالْيَمِينِ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
ثُمَّ لَقَطَعْنَا مِنْهُ الْوَتِينَ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
فَمَا مِنكُم مِّنْ أَحَدٍ عَنْهُ حَاجِزِينَ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
وَإِنَّهُ لَتَذْكِرَةٌ لِّلْمُتَّقِينَ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
وَإِنَّا لَنَعْلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
وَإِنَّهُ لَحَسْرَةٌ عَلَى الْكَافِرِينَ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
وَإِنَّهُ لَحَقُّ الْيَقِينِ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
← 68 አል-ሀቅቃ (69/114) 70 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ሀቅቃ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

69الحاقة Al-Haqqah 📚 52 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ሀቅቃ — 52 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers