ሱረቱ አል-ሙደተሲር
PDF —
Built right in your browser — download starts automatically
ሱረቱ አል-ሙደተሲር pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አል-ሙደተሲር pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ሙደተሲር ትርጉም. አል-ሙደተሲር (Meccan) 56 አንቀጽ.
Related
- አል-ሙደተሲር ትርጉምአማርኛ
- አል-ሙደተሲር mp3ስሙ
- Quran Index አማርኛ114
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አል-ሙደተሲር

ﮪﮫﮬ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
ﮭﮮﮯ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
ﮰﮱﯓ
ጌታህንም አክብር፡፡
ﯔﯕﯖ
ልብስህንም አጥራ፡፡
ﯗﯘﯙ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
ﯚﯛﯜﯝ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
ﯞﯟﯠ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴ
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
ﯺﯻﯼ
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
ﯽﯾﯿﰀ
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
ﰍﰎﰏ
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
ﰐﰑﰒﰓ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
ﭑﭒﭓﭔ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
ﭕﭖﭗﭘﭙ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
ﭚﭛﭜ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
ﭝﭞﭟﭠ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
ﭡﭢﭣﭤ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
ﭲﭳﭴ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
ﭺﭻﭼﭽﭾ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
ﭿﮀﮁ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
ﮂﮃﮄﮅ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
ﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
ﯥﯦﯧ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
ﯨﯩﯪﯫ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
ﯬﯭﯮﯯ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
ﯰﯱﯲﯳ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
ﯴﯵﯶ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
ﯿﰀﰁﰂﰃﰄ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
ﰅﰆﰇﰈ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﰉﰊﰋﰌ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
ﰍﰎﰏ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
ﰐﰑﰒﰓﰔ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
ﰕﰖﰗﰘﰙﰚ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
ﰛﰜﰝﰞﰟ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
ﰠﰡﰢﰣﰤ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
ﰥﰦﰧﰨﰩ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
ﰪﰫﰬﰭ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
ﭑﭒﭓﭔﭕ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
ﭜﭝﭞﭟ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
ﭠﭡﭢﭣ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
ﭵﭶﭷﭸ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
ﭹﭺﭻﭼ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Tuesday, August 18, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







