ሱረቱ አል-ሙደተሲር ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ሙደተሲርን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (56 አንቀጽ — مكية). አል-ሙደተሲር ስሙ, አል-ሙደተሲር ትርጉም, አል-ሙደተሲር mp3, አል-ሙደተሲር pdf.

ሱረቱ አል-ሙደተሲርን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
يَا أَيُّهَا الْمُدَّثِّرُ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
قُمْ فَأَنذِرْ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
وَرَبَّكَ فَكَبِّرْ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ጌታህንም አክብር፡፡
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرْ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ልብስህንም አጥራ፡፡
وَالرُّجْزَ فَاهْجُرْ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ጣዖትንም ራቅ፡፡
وَلَا تَمْنُن تَسْتَكْثِرُ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
وَلِرَبِّكَ فَاصْبِرْ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
فَإِذَا نُقِرَ فِي النَّاقُورِ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
فَذَٰلِكَ يَوْمَئِذٍ يَوْمٌ عَسِيرٌ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
عَلَى الْكَافِرِينَ غَيْرُ يَسِيرٍ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
ذَرْنِي وَمَنْ خَلَقْتُ وَحِيدًا ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
وَجَعَلْتُ لَهُ مَالًا مَّمْدُودًا ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
وَبَنِينَ شُهُودًا ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
وَمَهَّدتُّ لَهُ تَمْهِيدًا ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
ثُمَّ يَطْمَعُ أَنْ أَزِيدَ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
كَلَّا ۖ إِنَّهُ كَانَ لِآيَاتِنَا عَنِيدًا ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
سَأُرْهِقُهُ صَعُودًا ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
إِنَّهُ فَكَّرَ وَقَدَّرَ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
فَقُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
ثُمَّ قُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
ثُمَّ نَظَرَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
ثُمَّ أَدْبَرَ وَاسْتَكْبَرَ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
فَقَالَ إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ يُؤْثَرُ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
إِنْ هَٰذَا إِلَّا قَوْلُ الْبَشَرِ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
سَأُصْلِيهِ سَقَرَ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا سَقَرُ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
لَا تُبْقِي وَلَا تَذَرُ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
لَوَّاحَةٌ لِّلْبَشَرِ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
عَلَيْهَا تِسْعَةَ عَشَرَ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
وَمَا جَعَلْنَا أَصْحَابَ النَّارِ إِلَّا مَلَائِكَةً ۙ وَمَا جَعَلْنَا عِدَّتَهُمْ إِلَّا فِتْنَةً لِّلَّذِينَ كَفَرُوا لِيَسْتَيْقِنَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَيَزْدَادَ الَّذِينَ آمَنُوا إِيمَانًا ۙ وَلَا يَرْتَابَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَالْمُؤْمِنُونَ ۙ وَلِيَقُولَ الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٌ وَالْكَافِرُونَ مَاذَا أَرَادَ اللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلًا ۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ اللَّهُ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي مَن يَشَاءُ ۚ وَمَا يَعْلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَ ۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْبَشَرِ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
كَلَّا وَالْقَمَرِ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
وَاللَّيْلِ إِذْ أَدْبَرَ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
وَالصُّبْحِ إِذَا أَسْفَرَ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
إِنَّهَا لَإِحْدَى الْكُبَرِ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
نَذِيرًا لِّلْبَشَرِ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَتَقَدَّمَ أَوْ يَتَأَخَّرَ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
كُلُّ نَفْسٍ بِمَا كَسَبَتْ رَهِينَةٌ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
إِلَّا أَصْحَابَ الْيَمِينِ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
فِي جَنَّاتٍ يَتَسَاءَلُونَ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
عَنِ الْمُجْرِمِينَ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
مَا سَلَكَكُمْ فِي سَقَرَ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
قَالُوا لَمْ نَكُ مِنَ الْمُصَلِّينَ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
فَمَا تَنفَعُهُمْ شَفَاعَةُ الشَّافِعِينَ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
فَمَا لَهُمْ عَنِ التَّذْكِرَةِ مُعْرِضِينَ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
كَأَنَّهُمْ حُمُرٌ مُّسْتَنفِرَةٌ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
فَرَّتْ مِن قَسْوَرَةٍ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
بَلْ يُرِيدُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُؤْتَىٰ صُحُفًا مُّنَشَّرَةً ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
كَلَّا ۖ بَل لَّا يَخَافُونَ الْآخِرَةَ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
كَلَّا إِنَّهُ تَذْكِرَةٌ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
فَمَن شَاءَ ذَكَرَهُ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
وَمَا يَذْكُرُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ ۚ هُوَ أَهْلُ التَّقْوَىٰ وَأَهْلُ الْمَغْفِرَةِ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
← 73 አል-ሙደተሲር (74/114) 75 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ሙደተሲር አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

74المدثر Al-Muddaththir 📚 56 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ሙደተሲር — 56 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers