Surah An-Najm with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Najm | النجم - Ayat Count 62 - The number of the surah in moshaf: 53 - The meaning of the surah in English: The Star.

وَالنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ(1)

 በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَىٰ(2)

 ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

وَمَا يَنطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ(3)

 ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡

إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ(4)

 እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

عَلَّمَهُ شَدِيدُ الْقُوَىٰ(5)

 ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡

ذُو مِرَّةٍ فَاسْتَوَىٰ(6)

 የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡

وَهُوَ بِالْأُفُقِ الْأَعْلَىٰ(7)

 እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ(8)

 ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡

فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ(9)

 (ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

فَأَوْحَىٰ إِلَىٰ عَبْدِهِ مَا أَوْحَىٰ(10)

 ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡

مَا كَذَبَ الْفُؤَادُ مَا رَأَىٰ(11)

 (ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡

أَفَتُمَارُونَهُ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ(12)

 ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?

وَلَقَدْ رَآهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ(13)

 በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡

عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَىٰ(14)

 በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤

عِندَهَا جَنَّةُ الْمَأْوَىٰ(15)

 እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

إِذْ يَغْشَى السِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ(16)

 ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

مَا زَاغَ الْبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ(17)

 ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡

لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ آيَاتِ رَبِّهِ الْكُبْرَىٰ(18)

 ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡

أَفَرَأَيْتُمُ اللَّاتَ وَالْعُزَّىٰ(19)

 አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?

وَمَنَاةَ الثَّالِثَةَ الْأُخْرَىٰ(20)

 ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)

أَلَكُمُ الذَّكَرُ وَلَهُ الْأُنثَىٰ(21)

 ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?

تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰ(22)

 ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡

إِنْ هِيَ إِلَّا أَسْمَاءٌ سَمَّيْتُمُوهَا أَنتُمْ وَآبَاؤُكُم مَّا أَنزَلَ اللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَانٍ ۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ وَمَا تَهْوَى الْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَاءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ الْهُدَىٰ(23)

 እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡

أَمْ لِلْإِنسَانِ مَا تَمَنَّىٰ(24)

 ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?

فَلِلَّهِ الْآخِرَةُ وَالْأُولَىٰ(25)

 መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

۞ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ(26)

 በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡

إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِالْآخِرَةِ لَيُسَمُّونَ الْمَلَائِكَةَ تَسْمِيَةَ الْأُنثَىٰ(27)

 እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

وَمَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ ۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ ۖ وَإِنَّ الظَّنَّ لَا يُغْنِي مِنَ الْحَقِّ شَيْئًا(28)

 ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡

فَأَعْرِضْ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكْرِنَا وَلَمْ يُرِدْ إِلَّا الْحَيَاةَ الدُّنْيَا(29)

 ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ذَٰلِكَ مَبْلَغُهُم مِّنَ الْعِلْمِ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اهْتَدَىٰ(30)

 ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

وَلِلَّهِ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ لِيَجْزِيَ الَّذِينَ أَسَاءُوا بِمَا عَمِلُوا وَيَجْزِيَ الَّذِينَ أَحْسَنُوا بِالْحُسْنَى(31)

 በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡

الَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَائِرَ الْإِثْمِ وَالْفَوَاحِشَ إِلَّا اللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَاسِعُ الْمَغْفِرَةِ ۚ هُوَ أَعْلَمُ بِكُمْ إِذْ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَإِذْ أَنتُمْ أَجِنَّةٌ فِي بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ ۖ فَلَا تُزَكُّوا أَنفُسَكُمْ ۖ هُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اتَّقَىٰ(32)

 (እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

أَفَرَأَيْتَ الَّذِي تَوَلَّىٰ(33)

 ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?

وَأَعْطَىٰ قَلِيلًا وَأَكْدَىٰ(34)

 ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

أَعِندَهُ عِلْمُ الْغَيْبِ فَهُوَ يَرَىٰ(35)

 የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

أَمْ لَمْ يُنَبَّأْ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ(36)

 ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?

وَإِبْرَاهِيمَ الَّذِي وَفَّىٰ(37)

 በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ(38)

 (እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡

وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَانِ إِلَّا مَا سَعَىٰ(39)

 ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡

وَأَنَّ سَعْيَهُ سَوْفَ يُرَىٰ(40)

 ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡

ثُمَّ يُجْزَاهُ الْجَزَاءَ الْأَوْفَىٰ(41)

 ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡

وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ الْمُنتَهَىٰ(42)

 መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَضْحَكَ وَأَبْكَىٰ(43)

 እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَمَاتَ وَأَحْيَا(44)

 እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡

وَأَنَّهُ خَلَقَ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ(45)

 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡

مِن نُّطْفَةٍ إِذَا تُمْنَىٰ(46)

 ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡

وَأَنَّ عَلَيْهِ النَّشْأَةَ الْأُخْرَىٰ(47)

 የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَغْنَىٰ وَأَقْنَىٰ(48)

 እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ رَبُّ الشِّعْرَىٰ(49)

 እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡

وَأَنَّهُ أَهْلَكَ عَادًا الْأُولَىٰ(50)

 እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡

وَثَمُودَ فَمَا أَبْقَىٰ(51)

 ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

وَقَوْمَ نُوحٍ مِّن قَبْلُ ۖ إِنَّهُمْ كَانُوا هُمْ أَظْلَمَ وَأَطْغَىٰ(52)

 በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡

وَالْمُؤْتَفِكَةَ أَهْوَىٰ(53)

 የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡

فَغَشَّاهَا مَا غَشَّىٰ(54)

 ያለበሳትንም አለበሳት፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ(55)

 ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

هَٰذَا نَذِيرٌ مِّنَ النُّذُرِ الْأُولَىٰ(56)

 ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡

أَزِفَتِ الْآزِفَةُ(57)

 ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡

لَيْسَ لَهَا مِن دُونِ اللَّهِ كَاشِفَةٌ(58)

 ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡

أَفَمِنْ هَٰذَا الْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ(59)

 ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?

وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ(60)

 ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?

وَأَنتُمْ سَامِدُونَ(61)

 እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡

فَاسْجُدُوا لِلَّهِ وَاعْبُدُوا ۩(62)

 ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah An-Najm with the voice of the most famous Quran reciters :

surah An-Najm mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter An-Najm Complete with high quality
surah An-Najm Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah An-Najm Bandar Balila
Bandar Balila
surah An-Najm Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah An-Najm Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah An-Najm Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah An-Najm Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah An-Najm Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah An-Najm Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah An-Najm Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah An-Najm Fares Abbad
Fares Abbad
surah An-Najm Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah An-Najm Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah An-Najm Al Hosary
Al Hosary
surah An-Najm Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah An-Najm Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب