ሱረቱ አል-ቂያማ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አል-ቂያማን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (40 አንቀጽ — مكية). አል-ቂያማ ስሙ, አል-ቂያማ ትርጉም, አል-ቂያማ mp3, አል-ቂያማ pdf.

ሱረቱ አል-ቂያማን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
لَا أُقْسِمُ بِيَوْمِ الْقِيَامَةِ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَلَّن نَّجْمَعَ عِظَامَهُ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
بَلَىٰ قَادِرِينَ عَلَىٰ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
بَلْ يُرِيدُ الْإِنسَانُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
يَسْأَلُ أَيَّانَ يَوْمُ الْقِيَامَةِ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
فَإِذَا بَرِقَ الْبَصَرُ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
وَخَسَفَ الْقَمَرُ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
وَجُمِعَ الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
يَقُولُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ الْمَفَرُّ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
كَلَّا لَا وَزَرَ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمُسْتَقَرُّ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
يُنَبَّأُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
بَلِ الْإِنسَانُ عَلَىٰ نَفْسِهِ بَصِيرَةٌ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
وَلَوْ أَلْقَىٰ مَعَاذِيرَهُ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
لَا تُحَرِّكْ بِهِ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُ وَقُرْآنَهُ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
فَإِذَا قَرَأْنَاهُ فَاتَّبِعْ قُرْآنَهُ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ الْعَاجِلَةَ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
وَتَذَرُونَ الْآخِرَةَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ نَّاضِرَةٌ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ بَاسِرَةٌ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
كَلَّا إِذَا بَلَغَتِ التَّرَاقِيَ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
وَقِيلَ مَنْ ۜ رَاقٍ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
وَظَنَّ أَنَّهُ الْفِرَاقُ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
وَالْتَفَّتِ السَّاقُ بِالسَّاقِ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمَسَاقُ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰ أَهْلِهِ يَتَمَطَّىٰ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
ثُمَّ أَوْلَىٰ لَكَ فَأَوْلَىٰ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
أَلَمْ يَكُ نُطْفَةً مِّن مَّنِيٍّ يُمْنَىٰ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةً فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
فَجَعَلَ مِنْهُ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
أَلَيْسَ ذَٰلِكَ بِقَادِرٍ عَلَىٰ أَن يُحْيِيَ الْمَوْتَىٰ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
← 74 አል-ቂያማ (75/114) 76 →
ማንበብ ሱረቱ አል-ቂያማ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

75القيامة Al-Qiyamah 📚 40 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አል-ቂያማ — 40 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers