سورة القلم بالأمهرية

  1. استمع للسورة
  2. سور أخرى
  3. ترجمة السورة
القرآن الكريم | ترجمة معاني القرآن | اللغة الأمهرية | سورة القلم | Qalam - عدد آياتها 52 - رقم السورة في المصحف: 68 - معنى السورة بالإنجليزية: The Pen.

ن ۚ وَالْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ(1)

ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡

مَا أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ(2)

አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡

وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍ(3)

ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡

وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍ(4)

አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡

فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ(5)

ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡

بِأَييِّكُمُ الْمَفْتُونُ(6)

ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡

إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِالْمُهْتَدِينَ(7)

ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡

فَلَا تُطِعِ الْمُكَذِّبِينَ(8)

ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡

وَدُّوا لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ(9)

ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡

وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍ مَّهِينٍ(10)

ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡

هَمَّازٍ مَّشَّاءٍ بِنَمِيمٍ(11)

ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡

مَّنَّاعٍ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ(12)

ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤

عُتُلٍّ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ(13)

ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡

أَن كَانَ ذَا مَالٍ وَبَنِينَ(14)

የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡

إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ(15)

በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

سَنَسِمُهُ عَلَى الْخُرْطُومِ(16)

በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡

إِنَّا بَلَوْنَاهُمْ كَمَا بَلَوْنَا أَصْحَابَ الْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ(17)

እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡

وَلَا يَسْتَثْنُونَ(18)

(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡

فَطَافَ عَلَيْهَا طَائِفٌ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَائِمُونَ(19)

እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡

فَأَصْبَحَتْ كَالصَّرِيمِ(20)

እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡

فَتَنَادَوْا مُصْبِحِينَ(21)

ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡

أَنِ اغْدُوا عَلَىٰ حَرْثِكُمْ إِن كُنتُمْ صَارِمِينَ(22)

«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡

فَانطَلَقُوا وَهُمْ يَتَخَافَتُونَ(23)

እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡

أَن لَّا يَدْخُلَنَّهَا الْيَوْمَ عَلَيْكُم مِّسْكِينٌ(24)

ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡

وَغَدَوْا عَلَىٰ حَرْدٍ قَادِرِينَ(25)

(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡

فَلَمَّا رَأَوْهَا قَالُوا إِنَّا لَضَالُّونَ(26)

(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ(27)

«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡

قَالَ أَوْسَطُهُمْ أَلَمْ أَقُل لَّكُمْ لَوْلَا تُسَبِّحُونَ(28)

ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡

قَالُوا سُبْحَانَ رَبِّنَا إِنَّا كُنَّا ظَالِمِينَ(29)

«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡

فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَلَاوَمُونَ(30)

የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡

قَالُوا يَا وَيْلَنَا إِنَّا كُنَّا طَاغِينَ(31)

«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡

عَسَىٰ رَبُّنَا أَن يُبْدِلَنَا خَيْرًا مِّنْهَا إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا رَاغِبُونَ(32)

«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡

كَذَٰلِكَ الْعَذَابُ ۖ وَلَعَذَابُ الْآخِرَةِ أَكْبَرُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ(33)

ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡

إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّاتِ النَّعِيمِ(34)

ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡

أَفَنَجْعَلُ الْمُسْلِمِينَ كَالْمُجْرِمِينَ(35)

ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?

مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ(36)

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡

أَمْ لَكُمْ كِتَابٌ فِيهِ تَدْرُسُونَ(37)

በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?

إِنَّ لَكُمْ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ(38)

በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)

أَمْ لَكُمْ أَيْمَانٌ عَلَيْنَا بَالِغَةٌ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۙ إِنَّ لَكُمْ لَمَا تَحْكُمُونَ(39)

ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?

سَلْهُمْ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ(40)

በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡

أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ فَلْيَأْتُوا بِشُرَكَائِهِمْ إِن كَانُوا صَادِقِينَ(41)

ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡

يَوْمَ يُكْشَفُ عَن سَاقٍ وَيُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ فَلَا يَسْتَطِيعُونَ(42)

ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۖ وَقَدْ كَانُوا يُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ وَهُمْ سَالِمُونَ(43)

ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡

فَذَرْنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا الْحَدِيثِ ۖ سَنَسْتَدْرِجُهُم مِّنْ حَيْثُ لَا يَعْلَمُونَ(44)

በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡

وَأُمْلِي لَهُمْ ۚ إِنَّ كَيْدِي مَتِينٌ(45)

እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡

أَمْ تَسْأَلُهُمْ أَجْرًا فَهُم مِّن مَّغْرَمٍ مُّثْقَلُونَ(46)

በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?

أَمْ عِندَهُمُ الْغَيْبُ فَهُمْ يَكْتُبُونَ(47)

ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?

فَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ الْحُوتِ إِذْ نَادَىٰ وَهُوَ مَكْظُومٌ(48)

ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡

لَّوْلَا أَن تَدَارَكَهُ نِعْمَةٌ مِّن رَّبِّهِ لَنُبِذَ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ مَذْمُومٌ(49)

ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡

فَاجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَجَعَلَهُ مِنَ الصَّالِحِينَ(50)

ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡

وَإِن يَكَادُ الَّذِينَ كَفَرُوا لَيُزْلِقُونَكَ بِأَبْصَارِهِمْ لَمَّا سَمِعُوا الذِّكْرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُ لَمَجْنُونٌ(51)

እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡

وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ(52)

ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡


المزيد من السور باللغة الأمهرية:

سورة البقرة آل عمران سورة النساء
سورة المائدة سورة يوسف سورة ابراهيم
سورة الحجر سورة الكهف سورة مريم
سورة السجدة سورة يس سورة الدخان
سورة النجم سورة الرحمن سورة الواقعة
سورة الحشر سورة الملك سورة الحاقة

تحميل سورة القلم بصوت أشهر القراء :

قم باختيار القارئ للاستماع و تحميل سورة القلم كاملة بجودة عالية
سورة القلم أحمد العجمي
أحمد العجمي
سورة القلم خالد الجليل
خالد الجليل
سورة القلم سعد الغامدي
سعد الغامدي
سورة القلم سعود الشريم
سعود الشريم
سورة القلم عبد الباسط عبد الصمد
عبد الباسط
سورة القلم عبد الله عواد الجهني
عبد الله الجهني
سورة القلم علي الحذيفي
علي الحذيفي
سورة القلم فارس عباد
فارس عباد
سورة القلم ماهر المعيقلي
ماهر المعيقلي
سورة القلم محمد جبريل
محمد جبريل
سورة القلم محمد صديق المنشاوي
المنشاوي
سورة القلم الحصري
الحصري
سورة القلم العفاسي
مشاري العفاسي
سورة القلم ناصر القطامي
ناصر القطامي
سورة القلم ياسر الدوسري
ياسر الدوسري



Wednesday, May 8, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب