ሱረቱ አን-ናዚዓት pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አን-ናዚዓት pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አን-ናዚዓት ትርጉም. ሱረቱ አን-ናዚዓት (Meccan) 46 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አን-ናዚዓት

ﮢﮣﮤ
79:1
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
ﮥﮦﮧ
79:2
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
ﮨﮩﮪ
79:3
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
ﮫﮬﮭ
79:4
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
ﮮﮯﮰ
79:5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
ﮱﯓﯔﯕ
79:6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
ﯖﯗﯘ
79:7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
ﯙﯚﯛﯜ
79:8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
ﯝﯞﯟ
79:9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
79:10
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
79:11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
79:12
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
ﯱﯲﯳﯴﯵ
79:13
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
ﯶﯷﯸﯹ
79:14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾ
79:15
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
ﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
79:16
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
79:17
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
ﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
79:18
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
ﭞﭟﭠﭡﭢ
79:19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
ﭣﭤﭥﭦ
79:20
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
ﭧﭨﭩ
79:21
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
ﭪﭫﭬﭭ
79:22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
ﭮﭯﭰ
79:23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵ
79:24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
ﭶﭷﭸﭹﭺﭻ
79:25
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
79:26
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
79:27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
ﮋﮌﮍﮎ
79:28
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓ
79:29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
ﮔﮕﮖﮗﮘ
79:30
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
ﮙﮚﮛﮜﮝ
79:31
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
ﮞﮟﮠ
79:32
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
ﮡﮢﮣﮤ
79:33
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩ
79:34
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
ﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
79:35
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
ﮰﮱﯓﯔﯕ
79:36
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
ﯖﯗﯘﯙ
79:37
የካደ ሰውማ፣
ﯚﯛﯜﯝ
79:38
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
ﯞﯟﯠﯡﯢ
79:39
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
79:40
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
ﯭﯮﯯﯰﯱ
79:41
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
79:42
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼ
79:43
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
ﯽﯾﯿﰀ
79:44
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆ
79:45
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
ﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐ
79:46
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







