Surah Al-Muddaththir with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Muddathir | المدثر - Ayat Count 56 - The number of the surah in moshaf: 74 - The meaning of the surah in English: The One Wrapped Up.

يَا أَيُّهَا الْمُدَّثِّرُ(1)

 አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!

قُمْ فَأَنذِرْ(2)

 ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡

وَرَبَّكَ فَكَبِّرْ(3)

 ጌታህንም አክብር፡፡

وَثِيَابَكَ فَطَهِّرْ(4)

 ልብስህንም አጥራ፡፡

وَالرُّجْزَ فَاهْجُرْ(5)

 ጣዖትንም ራቅ፡፡

وَلَا تَمْنُن تَسْتَكْثِرُ(6)

 ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ

وَلِرَبِّكَ فَاصْبِرْ(7)

 ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡

فَإِذَا نُقِرَ فِي النَّاقُورِ(8)

 በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡

فَذَٰلِكَ يَوْمَئِذٍ يَوْمٌ عَسِيرٌ(9)

 ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡

عَلَى الْكَافِرِينَ غَيْرُ يَسِيرٍ(10)

 በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡

ذَرْنِي وَمَنْ خَلَقْتُ وَحِيدًا(11)

 አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡

وَجَعَلْتُ لَهُ مَالًا مَّمْدُودًا(12)

 ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡

وَبَنِينَ شُهُودًا(13)

 (በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡

وَمَهَّدتُّ لَهُ تَمْهِيدًا(14)

 ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡

ثُمَّ يَطْمَعُ أَنْ أَزِيدَ(15)

 ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهُ كَانَ لِآيَاتِنَا عَنِيدًا(16)

 ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡

سَأُرْهِقُهُ صَعُودًا(17)

 በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡

إِنَّهُ فَكَّرَ وَقَدَّرَ(18)

 እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡

فَقُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ(19)

 ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ قُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ(20)

 ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ نَظَرَ(21)

 ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡

ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ(22)

 ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡

ثُمَّ أَدْبَرَ وَاسْتَكْبَرَ(23)

 ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡

فَقَالَ إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ يُؤْثَرُ(24)

 አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

إِنْ هَٰذَا إِلَّا قَوْلُ الْبَشَرِ(25)

 «ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»

سَأُصْلِيهِ سَقَرَ(26)

 በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا سَقَرُ(27)

 ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

لَا تُبْقِي وَلَا تَذَرُ(28)

 (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡

لَوَّاحَةٌ لِّلْبَشَرِ(29)

 ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡

عَلَيْهَا تِسْعَةَ عَشَرَ(30)

 በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

وَمَا جَعَلْنَا أَصْحَابَ النَّارِ إِلَّا مَلَائِكَةً ۙ وَمَا جَعَلْنَا عِدَّتَهُمْ إِلَّا فِتْنَةً لِّلَّذِينَ كَفَرُوا لِيَسْتَيْقِنَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَيَزْدَادَ الَّذِينَ آمَنُوا إِيمَانًا ۙ وَلَا يَرْتَابَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَالْمُؤْمِنُونَ ۙ وَلِيَقُولَ الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٌ وَالْكَافِرُونَ مَاذَا أَرَادَ اللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلًا ۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ اللَّهُ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي مَن يَشَاءُ ۚ وَمَا يَعْلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَ ۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْبَشَرِ(31)

 የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

كَلَّا وَالْقَمَرِ(32)

 (ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡

وَاللَّيْلِ إِذْ أَدْبَرَ(33)

 በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡

وَالصُّبْحِ إِذَا أَسْفَرَ(34)

 በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡

إِنَّهَا لَإِحْدَى الْكُبَرِ(35)

 እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡

نَذِيرًا لِّلْبَشَرِ(36)

 ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡

لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَتَقَدَّمَ أَوْ يَتَأَخَّرَ(37)

 ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡

كُلُّ نَفْسٍ بِمَا كَسَبَتْ رَهِينَةٌ(38)

 ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡

إِلَّا أَصْحَابَ الْيَمِينِ(39)

 የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡

فِي جَنَّاتٍ يَتَسَاءَلُونَ(40)

 (እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡

عَنِ الْمُجْرِمِينَ(41)

 ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡

مَا سَلَكَكُمْ فِي سَقَرَ(42)

 (ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

قَالُوا لَمْ نَكُ مِنَ الْمُصَلِّينَ(43)

 (እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡

وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ(44)

 «ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡

وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ(45)

 «ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡

وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ(46)

 «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡

حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ(47)

 «እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»

فَمَا تَنفَعُهُمْ شَفَاعَةُ الشَّافِعِينَ(48)

 የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡

فَمَا لَهُمْ عَنِ التَّذْكِرَةِ مُعْرِضِينَ(49)

 ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?

كَأَنَّهُمْ حُمُرٌ مُّسْتَنفِرَةٌ(50)

 እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

فَرَّتْ مِن قَسْوَرَةٍ(51)

 ከዐንበሳ የሸሹ፡፡

بَلْ يُرِيدُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُؤْتَىٰ صُحُفًا مُّنَشَّرَةً(52)

 ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡

كَلَّا ۖ بَل لَّا يَخَافُونَ الْآخِرَةَ(53)

 ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡

كَلَّا إِنَّهُ تَذْكِرَةٌ(54)

 ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡

فَمَن شَاءَ ذَكَرَهُ(55)

 ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

وَمَا يَذْكُرُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ ۚ هُوَ أَهْلُ التَّقْوَىٰ وَأَهْلُ الْمَغْفِرَةِ(56)

 አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah Al-Muddaththir with the voice of the most famous Quran reciters :

surah Al-Muddaththir mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter Al-Muddaththir Complete with high quality
surah Al-Muddaththir Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah Al-Muddaththir Bandar Balila
Bandar Balila
surah Al-Muddaththir Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah Al-Muddaththir Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah Al-Muddaththir Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah Al-Muddaththir Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah Al-Muddaththir Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah Al-Muddaththir Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah Al-Muddaththir Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah Al-Muddaththir Fares Abbad
Fares Abbad
surah Al-Muddaththir Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah Al-Muddaththir Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah Al-Muddaththir Al Hosary
Al Hosary
surah Al-Muddaththir Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah Al-Muddaththir Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Wednesday, May 8, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب