Surah Al-Haqqah with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Al-Haqqah | الحاقة - Ayat Count 52 - The number of the surah in moshaf: 69 - The meaning of the surah in English: The Sure Reality.

الْحَاقَّةُ(1)

 እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡

مَا الْحَاقَّةُ(2)

 አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!

وَمَا أَدْرَاكَ مَا الْحَاقَّةُ(3)

 አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

كَذَّبَتْ ثَمُودُ وَعَادٌ بِالْقَارِعَةِ(4)

 ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡

فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهْلِكُوا بِالطَّاغِيَةِ(5)

 ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

وَأَمَّا عَادٌ فَأُهْلِكُوا بِرِيحٍ صَرْصَرٍ عَاتِيَةٍ(6)

 ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

سَخَّرَهَا عَلَيْهِمْ سَبْعَ لَيَالٍ وَثَمَانِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومًا فَتَرَى الْقَوْمَ فِيهَا صَرْعَىٰ كَأَنَّهُمْ أَعْجَازُ نَخْلٍ خَاوِيَةٍ(7)

 ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

فَهَلْ تَرَىٰ لَهُم مِّن بَاقِيَةٍ(8)

 ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?

وَجَاءَ فِرْعَوْنُ وَمَن قَبْلَهُ وَالْمُؤْتَفِكَاتُ بِالْخَاطِئَةِ(9)

 ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

فَعَصَوْا رَسُولَ رَبِّهِمْ فَأَخَذَهُمْ أَخْذَةً رَّابِيَةً(10)

 የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

إِنَّا لَمَّا طَغَى الْمَاءُ حَمَلْنَاكُمْ فِي الْجَارِيَةِ(11)

 እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡

لِنَجْعَلَهَا لَكُمْ تَذْكِرَةً وَتَعِيَهَا أُذُنٌ وَاعِيَةٌ(12)

 ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡

فَإِذَا نُفِخَ فِي الصُّورِ نَفْخَةٌ وَاحِدَةٌ(13)

 በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡

وَحُمِلَتِ الْأَرْضُ وَالْجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةً وَاحِدَةً(14)

 ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡

فَيَوْمَئِذٍ وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ(15)

 በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡

وَانشَقَّتِ السَّمَاءُ فَهِيَ يَوْمَئِذٍ وَاهِيَةٌ(16)

 ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

وَالْمَلَكُ عَلَىٰ أَرْجَائِهَا ۚ وَيَحْمِلُ عَرْشَ رَبِّكَ فَوْقَهُمْ يَوْمَئِذٍ ثَمَانِيَةٌ(17)

 መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡

يَوْمَئِذٍ تُعْرَضُونَ لَا تَخْفَىٰ مِنكُمْ خَافِيَةٌ(18)

 በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

فَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ فَيَقُولُ هَاؤُمُ اقْرَءُوا كِتَابِيَهْ(19)

 መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡

إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَاقٍ حِسَابِيَهْ(20)

 «እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡

فَهُوَ فِي عِيشَةٍ رَّاضِيَةٍ(21)

 እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡

فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٍ(22)

 በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡

قُطُوفُهَا دَانِيَةٌ(23)

 ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡

كُلُوا وَاشْرَبُوا هَنِيئًا بِمَا أَسْلَفْتُمْ فِي الْأَيَّامِ الْخَالِيَةِ(24)

 በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡

وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِشِمَالِهِ فَيَقُولُ يَا لَيْتَنِي لَمْ أُوتَ كِتَابِيَهْ(25)

 መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡

وَلَمْ أَدْرِ مَا حِسَابِيَهْ(26)

 «ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡

يَا لَيْتَهَا كَانَتِ الْقَاضِيَةَ(27)

 «እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡

مَا أَغْنَىٰ عَنِّي مَالِيَهْ ۜ(28)

 «ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡

هَلَكَ عَنِّي سُلْطَانِيَهْ(29)

 «ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡

خُذُوهُ فَغُلُّوهُ(30)

 «ያዙት፤ እሰሩትም፡፡

ثُمَّ الْجَحِيمَ صَلُّوهُ(31)

 «ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡

ثُمَّ فِي سِلْسِلَةٍ ذَرْعُهَا سَبْعُونَ ذِرَاعًا فَاسْلُكُوهُ(32)

 «ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»

إِنَّهُ كَانَ لَا يُؤْمِنُ بِاللَّهِ الْعَظِيمِ(33)

 እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡

وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ الْمِسْكِينِ(34)

 ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡

فَلَيْسَ لَهُ الْيَوْمَ هَاهُنَا حَمِيمٌ(35)

 ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡

وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنْ غِسْلِينٍ(36)

 ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡

لَّا يَأْكُلُهُ إِلَّا الْخَاطِئُونَ(37)

 ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِمَا تُبْصِرُونَ(38)

 በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡

وَمَا لَا تُبْصِرُونَ(39)

 በማታዩትም ነገር፡፡

إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ(40)

 እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡

وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَاعِرٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تُؤْمِنُونَ(41)

 እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡

وَلَا بِقَوْلِ كَاهِنٍ ۚ قَلِيلًا مَّا تَذَكَّرُونَ(42)

 የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡

تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ(43)

 ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

وَلَوْ تَقَوَّلَ عَلَيْنَا بَعْضَ الْأَقَاوِيلِ(44)

 በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤

لَأَخَذْنَا مِنْهُ بِالْيَمِينِ(45)

 በኀይል በያዝነው ነበር፡፡

ثُمَّ لَقَطَعْنَا مِنْهُ الْوَتِينَ(46)

 ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡

فَمَا مِنكُم مِّنْ أَحَدٍ عَنْهُ حَاجِزِينَ(47)

 ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡

وَإِنَّهُ لَتَذْكِرَةٌ لِّلْمُتَّقِينَ(48)

 እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡

وَإِنَّا لَنَعْلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ(49)

 እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

وَإِنَّهُ لَحَسْرَةٌ عَلَى الْكَافِرِينَ(50)

 እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡

وَإِنَّهُ لَحَقُّ الْيَقِينِ(51)

 እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ(52)

 የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah Al-Haqqah with the voice of the most famous Quran reciters :

surah Al-Haqqah mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter Al-Haqqah Complete with high quality
surah Al-Haqqah Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah Al-Haqqah Bandar Balila
Bandar Balila
surah Al-Haqqah Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah Al-Haqqah Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah Al-Haqqah Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah Al-Haqqah Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah Al-Haqqah Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah Al-Haqqah Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah Al-Haqqah Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah Al-Haqqah Fares Abbad
Fares Abbad
surah Al-Haqqah Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah Al-Haqqah Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah Al-Haqqah Al Hosary
Al Hosary
surah Al-Haqqah Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah Al-Haqqah Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب