Mearic suresi çevirisi Amharca

  1. Suresi mp3
  2. Başka bir sure
  3. Amharca
Kuranı Kerim türkçe meali | Kur'an çevirileri | Amharca dili | Mearic Suresi | المعارج - Ayet sayısı 44 - Moshaf'taki surenin numarası: 70 - surenin ingilizce anlamı: The Ways of Ascent.

سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ(1)

 ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡

لِّلْكَافِرِينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ(2)

 በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡

مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ(3)

 የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ(4)

 መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡

فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا(5)

 መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡

إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا(6)

 እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡

وَنَرَاهُ قَرِيبًا(7)

 እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡

يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ(8)

 ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡

وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ(9)

 ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡

وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا(10)

 ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ(11)

 (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡

وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ(12)

 በሚስቱም በወንድሙም፡፡

وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ(13)

 በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡

وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ(14)

 በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ(15)

 ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡

نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ(16)

 የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡

تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ(17)

 (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡

وَجَمَعَ فَأَوْعَىٰ(18)

 ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡

۞ إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا(19)

 ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡

إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا(20)

 ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡

وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا(21)

 መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡

إِلَّا الْمُصَلِّينَ(22)

 ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡

الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ(23)

 እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ(24)

 እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡

لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ(25)

 ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡

وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ(26)

 እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡

وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ(27)

 እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡

إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ(28)

 የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ(29)

 እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

إِلَّا عَلَىٰ أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ(30)

 በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡

فَمَنِ ابْتَغَىٰ وَرَاءَ ذَٰلِكَ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْعَادُونَ(31)

 ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ(32)

 እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ(33)

 እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡

وَالَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ(34)

 እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡

أُولَٰئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ(35)

 እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡

فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ(36)

 ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ(37)

 ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡

أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ(38)

 ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

كَلَّا ۖ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ(39)

 ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡

فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ(40)

 በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ(41)

 ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّىٰ يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ(42)

 ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَىٰ نُصُبٍ يُوفِضُونَ(43)

 ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۚ ذَٰلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ(44)

 ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡


Amharca diğer sureler:

Bakara suresi Âl-i İmrân Nisâ suresi
Mâide suresi Yûsuf suresi İbrâhîm suresi
Hicr suresi Kehf suresi Meryem suresi
Hac suresi Kasas suresi Ankebût suresi
As-Sajdah Yâsîn suresi Duhân suresi
fetih suresi Hucurât suresi Kâf suresi
Necm suresi Rahmân suresi vakıa suresi
Haşr suresi Mülk suresi Hâkka suresi
İnşikâk suresi Alâ suresi Gâşiye suresi

En ünlü okuyucuların sesiyle Mearic Suresi indirin:

Surah Al-Maarij mp3: yüksek kalitede dinlemek ve indirmek için okuyucuyu seçerek
Mearic Suresi Ahmed El Agamy
Ahmed El Agamy
Mearic Suresi Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
Mearic Suresi Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
Mearic Suresi Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
Mearic Suresi Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
Mearic Suresi Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
Mearic Suresi Ali Al Hudhaifi
Ali Al Hudhaifi
Mearic Suresi Fares Abbad
Fares Abbad
Mearic Suresi Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
Mearic Suresi Muhammad Jibril
Muhammad Jibril
Mearic Suresi Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
Mearic Suresi Al Hosary
Al Hosary
Mearic Suresi Al-afasi
Mishari Al-afasi
Mearic Suresi Nasser Al Qatami
Nasser Al Qatami
Mearic Suresi Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Saturday, May 18, 2024

Bizim için dua et, teşekkürler