ሱረቱ አል-ቀላም pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አል-ቀላም pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ቀላም ትርጉም. ሱረቱ አል-ቀላም (Meccan) 52 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አል-ቀላም

ﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
68:1
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
68:2
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
68:3
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟ
68:4
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
ﮠﮡﮢ
68:5
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
ﮣﮤﮥ
68:6
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
68:7
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
ﯓﯔﯕﯖ
68:8
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛ
68:9
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
68:10
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
ﯢﯣﯤﯥ
68:11
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
68:12
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
ﯫﯬﯭﯮﯯ
68:13
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
68:14
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
68:15
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
ﯾﯿﰀﰁ
68:16
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
68:17
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
ﭜﭝﭞ
68:18
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
68:19
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
ﭧﭨﭩ
68:20
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
ﭪﭫﭬ
68:21
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
68:22
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
ﭵﭶﭷﭸ
68:23
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
68:24
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄ
68:25
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
68:26
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
ﮋﮌﮍﮎ
68:27
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
68:28
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
68:29
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
68:30
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
68:31
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕ
68:32
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
68:33
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
68:34
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
ﯨﯩﯪﯫ
68:35
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
ﯬﯭﯮﯯﯰ
68:36
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
ﯱﯲﯳﯴﯵﯶ
68:37
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼ
68:38
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
ﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
68:39
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
ﰊﰋﰌﰍﰎ
68:40
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
ﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
68:41
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
ﰘﰙﰚﰛﰜﰝﰞﰟﰠﰡ
68:42
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
68:43
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
68:44
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
68:45
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
68:46
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
68:47
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
68:48
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
68:49
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
68:50
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨ
68:51
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭﮮ
68:52
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







