PDF —
52 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ አል-ቀላም pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ አል-ቀላም pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አል-ቀላም ትርጉም. ሱረቱ አል-ቀላም (Meccan) 52 አንቀጽ.

← አል-ሙልክሱረቱ አል-ቀላም አል-ሀቅቃ →


52 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
68:1 ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
68:2 አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
68:3 ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟ
68:4 አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
ﮠﮡﮢ
68:5 ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
ﮣﮤﮥ
68:6 ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
68:7 ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
ﯓﯔﯕﯖ
68:8 ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛ
68:9 ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
68:10 ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
ﯢﯣﯤﯥ
68:11 ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
68:12 ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
ﯫﯬﯭﯮﯯ
68:13 ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
68:14 የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
68:15 በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
ﯾﯿﰀﰁ
68:16 በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
68:17 እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
ﭜﭝﭞ
68:18 (በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
68:19 እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
ﭧﭨﭩ
68:20 እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
ﭪﭫﭬ
68:21 ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
68:22 «ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
ﭵﭶﭷﭸ
68:23 እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
68:24 ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄ
68:25 (ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
68:26 (ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
ﮋﮌﮍﮎ
68:27 «ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
68:28 ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
68:29 «ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
68:30 የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
68:31 «ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕ
68:32 «ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
68:33 ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
68:34 ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
ﯨﯩﯪﯫ
68:35 ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
ﯬﯭﯮﯯﯰ
68:36 ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
ﯱﯲﯳﯴﯵﯶ
68:37 በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼ
68:38 በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
ﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
68:39 ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
ﰊﰋﰌﰍﰎ
68:40 በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
ﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
68:41 ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
ﰘﰙﰚﰛﰜﰝﰞﰟﰠﰡ
68:42 ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
68:43 ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
68:44 በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
68:45 እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
68:46 በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
68:47 ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
68:48 ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
68:49 ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
68:50 ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨ
68:51 እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭﮮ
68:52 ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Wednesday, September 9, 2026

Don't forget us in your sincere prayers