ሱረቱ አት-ተክዊር
PDF —
29 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ አት-ተክዊር pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ አት-ተክዊር pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አት-ተክዊር ትርጉም. አት-ተክዊር (Meccan) 29 አንቀጽ.



ሱረቱ አት-ተክዊር
29 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﭙﭚﭛﭜ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
ﭝﭞﭟﭠ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
ﭡﭢﭣﭤ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
ﭥﭦﭧﭨ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
ﭩﭪﭫﭬ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
ﭭﭮﭯﭰ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
ﭱﭲﭳﭴ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
ﭵﭶﭷﭸ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
ﭹﭺﭻﭼ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
ﭽﭾﭿﮀ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
ﮁﮂﮃﮄ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
ﮅﮆﮇﮈ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
ﮉﮊﮋﮌ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
ﮒﮓﮔﮕ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ﮖﮗﮘ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
ﮙﮚﮛﮜ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
ﮝﮞﮟﮠ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
ﮭﮮﮯﮰ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
ﮱﯓﯔﯕ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
ﯖﯗﯘﯙﯚ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
ﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
ﯧﯨﯩ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers