ሱረቱ አት-ተክዊር pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አት-ተክዊር pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አት-ተክዊር ትርጉም. ሱረቱ አት-ተክዊር (Meccan) 29 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አት-ተክዊር

ﭙﭚﭛﭜ
81:1
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
ﭝﭞﭟﭠ
81:2
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
ﭡﭢﭣﭤ
81:3
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
ﭥﭦﭧﭨ
81:4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
ﭩﭪﭫﭬ
81:5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
ﭭﭮﭯﭰ
81:6
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
ﭱﭲﭳﭴ
81:7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
ﭵﭶﭷﭸ
81:8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
ﭹﭺﭻﭼ
81:9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
ﭽﭾﭿﮀ
81:10
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
ﮁﮂﮃﮄ
81:11
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
ﮅﮆﮇﮈ
81:12
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
ﮉﮊﮋﮌ
81:13
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
ﮍﮎﮏﮐﮑ
81:14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
ﮒﮓﮔﮕ
81:15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ﮖﮗﮘ
81:16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
ﮙﮚﮛﮜ
81:17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
ﮝﮞﮟﮠ
81:18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
ﮡﮢﮣﮤﮥ
81:19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
81:20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
ﮭﮮﮯﮰ
81:21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
ﮱﯓﯔﯕ
81:22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
ﯖﯗﯘﯙﯚ
81:23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
ﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
81:24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
81:25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
ﯧﯨﯩ
81:26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
81:27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
81:28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
81:29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







