Necm suresi çevirisi Amharca

  1. Suresi mp3
  2. Başka bir sure
  3. Amharca
Kuranı Kerim türkçe meali | Kur'an çevirileri | Amharca dili | Necm Suresi | النجم - Ayet sayısı 62 - Moshaf'taki surenin numarası: 53 - surenin ingilizce anlamı: The Star.

وَالنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ(1)

 በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَىٰ(2)

 ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

وَمَا يَنطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ(3)

 ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡

إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ(4)

 እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

عَلَّمَهُ شَدِيدُ الْقُوَىٰ(5)

 ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡

ذُو مِرَّةٍ فَاسْتَوَىٰ(6)

 የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡

وَهُوَ بِالْأُفُقِ الْأَعْلَىٰ(7)

 እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ(8)

 ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡

فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ(9)

 (ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

فَأَوْحَىٰ إِلَىٰ عَبْدِهِ مَا أَوْحَىٰ(10)

 ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡

مَا كَذَبَ الْفُؤَادُ مَا رَأَىٰ(11)

 (ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡

أَفَتُمَارُونَهُ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ(12)

 ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?

وَلَقَدْ رَآهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ(13)

 በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡

عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَىٰ(14)

 በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤

عِندَهَا جَنَّةُ الْمَأْوَىٰ(15)

 እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

إِذْ يَغْشَى السِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ(16)

 ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

مَا زَاغَ الْبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ(17)

 ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡

لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ آيَاتِ رَبِّهِ الْكُبْرَىٰ(18)

 ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡

أَفَرَأَيْتُمُ اللَّاتَ وَالْعُزَّىٰ(19)

 አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?

وَمَنَاةَ الثَّالِثَةَ الْأُخْرَىٰ(20)

 ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)

أَلَكُمُ الذَّكَرُ وَلَهُ الْأُنثَىٰ(21)

 ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?

تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰ(22)

 ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡

إِنْ هِيَ إِلَّا أَسْمَاءٌ سَمَّيْتُمُوهَا أَنتُمْ وَآبَاؤُكُم مَّا أَنزَلَ اللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَانٍ ۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ وَمَا تَهْوَى الْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَاءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ الْهُدَىٰ(23)

 እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡

أَمْ لِلْإِنسَانِ مَا تَمَنَّىٰ(24)

 ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?

فَلِلَّهِ الْآخِرَةُ وَالْأُولَىٰ(25)

 መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

۞ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ(26)

 በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡

إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِالْآخِرَةِ لَيُسَمُّونَ الْمَلَائِكَةَ تَسْمِيَةَ الْأُنثَىٰ(27)

 እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

وَمَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ ۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ ۖ وَإِنَّ الظَّنَّ لَا يُغْنِي مِنَ الْحَقِّ شَيْئًا(28)

 ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡

فَأَعْرِضْ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكْرِنَا وَلَمْ يُرِدْ إِلَّا الْحَيَاةَ الدُّنْيَا(29)

 ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ذَٰلِكَ مَبْلَغُهُم مِّنَ الْعِلْمِ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اهْتَدَىٰ(30)

 ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

وَلِلَّهِ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ لِيَجْزِيَ الَّذِينَ أَسَاءُوا بِمَا عَمِلُوا وَيَجْزِيَ الَّذِينَ أَحْسَنُوا بِالْحُسْنَى(31)

 በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡

الَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَائِرَ الْإِثْمِ وَالْفَوَاحِشَ إِلَّا اللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَاسِعُ الْمَغْفِرَةِ ۚ هُوَ أَعْلَمُ بِكُمْ إِذْ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَإِذْ أَنتُمْ أَجِنَّةٌ فِي بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ ۖ فَلَا تُزَكُّوا أَنفُسَكُمْ ۖ هُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اتَّقَىٰ(32)

 (እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

أَفَرَأَيْتَ الَّذِي تَوَلَّىٰ(33)

 ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?

وَأَعْطَىٰ قَلِيلًا وَأَكْدَىٰ(34)

 ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

أَعِندَهُ عِلْمُ الْغَيْبِ فَهُوَ يَرَىٰ(35)

 የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

أَمْ لَمْ يُنَبَّأْ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ(36)

 ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?

وَإِبْرَاهِيمَ الَّذِي وَفَّىٰ(37)

 በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ(38)

 (እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡

وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَانِ إِلَّا مَا سَعَىٰ(39)

 ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡

وَأَنَّ سَعْيَهُ سَوْفَ يُرَىٰ(40)

 ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡

ثُمَّ يُجْزَاهُ الْجَزَاءَ الْأَوْفَىٰ(41)

 ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡

وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ الْمُنتَهَىٰ(42)

 መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَضْحَكَ وَأَبْكَىٰ(43)

 እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَمَاتَ وَأَحْيَا(44)

 እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡

وَأَنَّهُ خَلَقَ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ(45)

 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡

مِن نُّطْفَةٍ إِذَا تُمْنَىٰ(46)

 ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡

وَأَنَّ عَلَيْهِ النَّشْأَةَ الْأُخْرَىٰ(47)

 የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ أَغْنَىٰ وَأَقْنَىٰ(48)

 እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡

وَأَنَّهُ هُوَ رَبُّ الشِّعْرَىٰ(49)

 እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡

وَأَنَّهُ أَهْلَكَ عَادًا الْأُولَىٰ(50)

 እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡

وَثَمُودَ فَمَا أَبْقَىٰ(51)

 ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

وَقَوْمَ نُوحٍ مِّن قَبْلُ ۖ إِنَّهُمْ كَانُوا هُمْ أَظْلَمَ وَأَطْغَىٰ(52)

 በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡

وَالْمُؤْتَفِكَةَ أَهْوَىٰ(53)

 የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡

فَغَشَّاهَا مَا غَشَّىٰ(54)

 ያለበሳትንም አለበሳት፡፡

فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ(55)

 ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

هَٰذَا نَذِيرٌ مِّنَ النُّذُرِ الْأُولَىٰ(56)

 ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡

أَزِفَتِ الْآزِفَةُ(57)

 ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡

لَيْسَ لَهَا مِن دُونِ اللَّهِ كَاشِفَةٌ(58)

 ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡

أَفَمِنْ هَٰذَا الْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ(59)

 ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?

وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ(60)

 ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?

وَأَنتُمْ سَامِدُونَ(61)

 እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡

فَاسْجُدُوا لِلَّهِ وَاعْبُدُوا ۩(62)

 ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡


Amharca diğer sureler:

Bakara suresi Âl-i İmrân Nisâ suresi
Mâide suresi Yûsuf suresi İbrâhîm suresi
Hicr suresi Kehf suresi Meryem suresi
Hac suresi Kasas suresi Ankebût suresi
As-Sajdah Yâsîn suresi Duhân suresi
fetih suresi Hucurât suresi Kâf suresi
Necm suresi Rahmân suresi vakıa suresi
Haşr suresi Mülk suresi Hâkka suresi
İnşikâk suresi Alâ suresi Gâşiye suresi

En ünlü okuyucuların sesiyle Necm Suresi indirin:

Surah An-Najm mp3: yüksek kalitede dinlemek ve indirmek için okuyucuyu seçerek
Necm Suresi Ahmed El Agamy
Ahmed El Agamy
Necm Suresi Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
Necm Suresi Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
Necm Suresi Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
Necm Suresi Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
Necm Suresi Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
Necm Suresi Ali Al Hudhaifi
Ali Al Hudhaifi
Necm Suresi Fares Abbad
Fares Abbad
Necm Suresi Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
Necm Suresi Muhammad Jibril
Muhammad Jibril
Necm Suresi Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
Necm Suresi Al Hosary
Al Hosary
Necm Suresi Al-afasi
Mishari Al-afasi
Necm Suresi Nasser Al Qatami
Nasser Al Qatami
Necm Suresi Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Sunday, May 19, 2024

Bizim için dua et, teşekkürler