Kalem suresi çevirisi Amharca

  1. Suresi mp3
  2. Başka bir sure
  3. Amharca
Kuranı Kerim türkçe meali | Kur'an çevirileri | Amharca dili | Kalem Suresi | القلم - Ayet sayısı 52 - Moshaf'taki surenin numarası: 68 - surenin ingilizce anlamı: The Pen.

ن ۚ وَالْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ(1)

 ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡

مَا أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ(2)

 አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡

وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍ(3)

 ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡

وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍ(4)

 አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡

فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ(5)

 ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡

بِأَييِّكُمُ الْمَفْتُونُ(6)

 ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡

إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِالْمُهْتَدِينَ(7)

 ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡

فَلَا تُطِعِ الْمُكَذِّبِينَ(8)

 ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡

وَدُّوا لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ(9)

 ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡

وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍ مَّهِينٍ(10)

 ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡

هَمَّازٍ مَّشَّاءٍ بِنَمِيمٍ(11)

 ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡

مَّنَّاعٍ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ(12)

 ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤

عُتُلٍّ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ(13)

 ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡

أَن كَانَ ذَا مَالٍ وَبَنِينَ(14)

 የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡

إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ(15)

 በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

سَنَسِمُهُ عَلَى الْخُرْطُومِ(16)

 በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡

إِنَّا بَلَوْنَاهُمْ كَمَا بَلَوْنَا أَصْحَابَ الْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ(17)

 እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡

وَلَا يَسْتَثْنُونَ(18)

 (በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡

فَطَافَ عَلَيْهَا طَائِفٌ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَائِمُونَ(19)

 እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡

فَأَصْبَحَتْ كَالصَّرِيمِ(20)

 እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡

فَتَنَادَوْا مُصْبِحِينَ(21)

 ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡

أَنِ اغْدُوا عَلَىٰ حَرْثِكُمْ إِن كُنتُمْ صَارِمِينَ(22)

 «ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡

فَانطَلَقُوا وَهُمْ يَتَخَافَتُونَ(23)

 እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡

أَن لَّا يَدْخُلَنَّهَا الْيَوْمَ عَلَيْكُم مِّسْكِينٌ(24)

 ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡

وَغَدَوْا عَلَىٰ حَرْدٍ قَادِرِينَ(25)

 (ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡

فَلَمَّا رَأَوْهَا قَالُوا إِنَّا لَضَالُّونَ(26)

 (ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ(27)

 «ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡

قَالَ أَوْسَطُهُمْ أَلَمْ أَقُل لَّكُمْ لَوْلَا تُسَبِّحُونَ(28)

 ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡

قَالُوا سُبْحَانَ رَبِّنَا إِنَّا كُنَّا ظَالِمِينَ(29)

 «ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡

فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَلَاوَمُونَ(30)

 የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡

قَالُوا يَا وَيْلَنَا إِنَّا كُنَّا طَاغِينَ(31)

 «ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡

عَسَىٰ رَبُّنَا أَن يُبْدِلَنَا خَيْرًا مِّنْهَا إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا رَاغِبُونَ(32)

 «ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡

كَذَٰلِكَ الْعَذَابُ ۖ وَلَعَذَابُ الْآخِرَةِ أَكْبَرُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ(33)

 ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡

إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّاتِ النَّعِيمِ(34)

 ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡

أَفَنَجْعَلُ الْمُسْلِمِينَ كَالْمُجْرِمِينَ(35)

 ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?

مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ(36)

 ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡

أَمْ لَكُمْ كِتَابٌ فِيهِ تَدْرُسُونَ(37)

 በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?

إِنَّ لَكُمْ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ(38)

 በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)

أَمْ لَكُمْ أَيْمَانٌ عَلَيْنَا بَالِغَةٌ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۙ إِنَّ لَكُمْ لَمَا تَحْكُمُونَ(39)

 ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?

سَلْهُمْ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ(40)

 በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡

أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ فَلْيَأْتُوا بِشُرَكَائِهِمْ إِن كَانُوا صَادِقِينَ(41)

 ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡

يَوْمَ يُكْشَفُ عَن سَاقٍ وَيُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ فَلَا يَسْتَطِيعُونَ(42)

 ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡

خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ۖ وَقَدْ كَانُوا يُدْعَوْنَ إِلَى السُّجُودِ وَهُمْ سَالِمُونَ(43)

 ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡

فَذَرْنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا الْحَدِيثِ ۖ سَنَسْتَدْرِجُهُم مِّنْ حَيْثُ لَا يَعْلَمُونَ(44)

 በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡

وَأُمْلِي لَهُمْ ۚ إِنَّ كَيْدِي مَتِينٌ(45)

 እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡

أَمْ تَسْأَلُهُمْ أَجْرًا فَهُم مِّن مَّغْرَمٍ مُّثْقَلُونَ(46)

 በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?

أَمْ عِندَهُمُ الْغَيْبُ فَهُمْ يَكْتُبُونَ(47)

 ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?

فَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ الْحُوتِ إِذْ نَادَىٰ وَهُوَ مَكْظُومٌ(48)

 ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡

لَّوْلَا أَن تَدَارَكَهُ نِعْمَةٌ مِّن رَّبِّهِ لَنُبِذَ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ مَذْمُومٌ(49)

 ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡

فَاجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَجَعَلَهُ مِنَ الصَّالِحِينَ(50)

 ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡

وَإِن يَكَادُ الَّذِينَ كَفَرُوا لَيُزْلِقُونَكَ بِأَبْصَارِهِمْ لَمَّا سَمِعُوا الذِّكْرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُ لَمَجْنُونٌ(51)

 እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡

وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ(52)

 ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡


Amharca diğer sureler:

Bakara suresi Âl-i İmrân Nisâ suresi
Mâide suresi Yûsuf suresi İbrâhîm suresi
Hicr suresi Kehf suresi Meryem suresi
Hac suresi Kasas suresi Ankebût suresi
As-Sajdah Yâsîn suresi Duhân suresi
fetih suresi Hucurât suresi Kâf suresi
Necm suresi Rahmân suresi vakıa suresi
Haşr suresi Mülk suresi Hâkka suresi
İnşikâk suresi Alâ suresi Gâşiye suresi

En ünlü okuyucuların sesiyle Kalem Suresi indirin:

Surah Al-Qalam mp3: yüksek kalitede dinlemek ve indirmek için okuyucuyu seçerek
Kalem Suresi Ahmed El Agamy
Ahmed El Agamy
Kalem Suresi Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
Kalem Suresi Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
Kalem Suresi Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
Kalem Suresi Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
Kalem Suresi Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
Kalem Suresi Ali Al Hudhaifi
Ali Al Hudhaifi
Kalem Suresi Fares Abbad
Fares Abbad
Kalem Suresi Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
Kalem Suresi Muhammad Jibril
Muhammad Jibril
Kalem Suresi Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
Kalem Suresi Al Hosary
Al Hosary
Kalem Suresi Al-afasi
Mishari Al-afasi
Kalem Suresi Nasser Al Qatami
Nasser Al Qatami
Kalem Suresi Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Sunday, May 19, 2024

Bizim için dua et, teşekkürler