Müddessir suresi çevirisi Amharca

  1. Suresi mp3
  2. Başka bir sure
  3. Amharca
Kuranı Kerim türkçe meali | Kur'an çevirileri | Amharca dili | Müddessir Suresi | المدثر - Ayet sayısı 56 - Moshaf'taki surenin numarası: 74 - surenin ingilizce anlamı: The One Wrapped Up.

يَا أَيُّهَا الْمُدَّثِّرُ(1)

 አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!

قُمْ فَأَنذِرْ(2)

 ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡

وَرَبَّكَ فَكَبِّرْ(3)

 ጌታህንም አክብር፡፡

وَثِيَابَكَ فَطَهِّرْ(4)

 ልብስህንም አጥራ፡፡

وَالرُّجْزَ فَاهْجُرْ(5)

 ጣዖትንም ራቅ፡፡

وَلَا تَمْنُن تَسْتَكْثِرُ(6)

 ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ

وَلِرَبِّكَ فَاصْبِرْ(7)

 ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡

فَإِذَا نُقِرَ فِي النَّاقُورِ(8)

 በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡

فَذَٰلِكَ يَوْمَئِذٍ يَوْمٌ عَسِيرٌ(9)

 ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡

عَلَى الْكَافِرِينَ غَيْرُ يَسِيرٍ(10)

 በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡

ذَرْنِي وَمَنْ خَلَقْتُ وَحِيدًا(11)

 አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡

وَجَعَلْتُ لَهُ مَالًا مَّمْدُودًا(12)

 ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡

وَبَنِينَ شُهُودًا(13)

 (በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡

وَمَهَّدتُّ لَهُ تَمْهِيدًا(14)

 ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡

ثُمَّ يَطْمَعُ أَنْ أَزِيدَ(15)

 ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡

كَلَّا ۖ إِنَّهُ كَانَ لِآيَاتِنَا عَنِيدًا(16)

 ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡

سَأُرْهِقُهُ صَعُودًا(17)

 በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡

إِنَّهُ فَكَّرَ وَقَدَّرَ(18)

 እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡

فَقُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ(19)

 ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ قُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ(20)

 ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!

ثُمَّ نَظَرَ(21)

 ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡

ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ(22)

 ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡

ثُمَّ أَدْبَرَ وَاسْتَكْبَرَ(23)

 ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡

فَقَالَ إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ يُؤْثَرُ(24)

 አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

إِنْ هَٰذَا إِلَّا قَوْلُ الْبَشَرِ(25)

 «ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»

سَأُصْلِيهِ سَقَرَ(26)

 በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡

وَمَا أَدْرَاكَ مَا سَقَرُ(27)

 ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

لَا تُبْقِي وَلَا تَذَرُ(28)

 (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡

لَوَّاحَةٌ لِّلْبَشَرِ(29)

 ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡

عَلَيْهَا تِسْعَةَ عَشَرَ(30)

 በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

وَمَا جَعَلْنَا أَصْحَابَ النَّارِ إِلَّا مَلَائِكَةً ۙ وَمَا جَعَلْنَا عِدَّتَهُمْ إِلَّا فِتْنَةً لِّلَّذِينَ كَفَرُوا لِيَسْتَيْقِنَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَيَزْدَادَ الَّذِينَ آمَنُوا إِيمَانًا ۙ وَلَا يَرْتَابَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَالْمُؤْمِنُونَ ۙ وَلِيَقُولَ الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٌ وَالْكَافِرُونَ مَاذَا أَرَادَ اللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلًا ۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ اللَّهُ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي مَن يَشَاءُ ۚ وَمَا يَعْلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَ ۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْبَشَرِ(31)

 የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

كَلَّا وَالْقَمَرِ(32)

 (ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡

وَاللَّيْلِ إِذْ أَدْبَرَ(33)

 በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡

وَالصُّبْحِ إِذَا أَسْفَرَ(34)

 በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡

إِنَّهَا لَإِحْدَى الْكُبَرِ(35)

 እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡

نَذِيرًا لِّلْبَشَرِ(36)

 ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡

لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَتَقَدَّمَ أَوْ يَتَأَخَّرَ(37)

 ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡

كُلُّ نَفْسٍ بِمَا كَسَبَتْ رَهِينَةٌ(38)

 ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡

إِلَّا أَصْحَابَ الْيَمِينِ(39)

 የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡

فِي جَنَّاتٍ يَتَسَاءَلُونَ(40)

 (እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡

عَنِ الْمُجْرِمِينَ(41)

 ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡

مَا سَلَكَكُمْ فِي سَقَرَ(42)

 (ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

قَالُوا لَمْ نَكُ مِنَ الْمُصَلِّينَ(43)

 (እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡

وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ(44)

 «ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡

وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ(45)

 «ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡

وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ(46)

 «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡

حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ(47)

 «እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»

فَمَا تَنفَعُهُمْ شَفَاعَةُ الشَّافِعِينَ(48)

 የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡

فَمَا لَهُمْ عَنِ التَّذْكِرَةِ مُعْرِضِينَ(49)

 ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?

كَأَنَّهُمْ حُمُرٌ مُّسْتَنفِرَةٌ(50)

 እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

فَرَّتْ مِن قَسْوَرَةٍ(51)

 ከዐንበሳ የሸሹ፡፡

بَلْ يُرِيدُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُؤْتَىٰ صُحُفًا مُّنَشَّرَةً(52)

 ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡

كَلَّا ۖ بَل لَّا يَخَافُونَ الْآخِرَةَ(53)

 ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡

كَلَّا إِنَّهُ تَذْكِرَةٌ(54)

 ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡

فَمَن شَاءَ ذَكَرَهُ(55)

 ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

وَمَا يَذْكُرُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ ۚ هُوَ أَهْلُ التَّقْوَىٰ وَأَهْلُ الْمَغْفِرَةِ(56)

 አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡


Amharca diğer sureler:

Bakara suresi Âl-i İmrân Nisâ suresi
Mâide suresi Yûsuf suresi İbrâhîm suresi
Hicr suresi Kehf suresi Meryem suresi
Hac suresi Kasas suresi Ankebût suresi
As-Sajdah Yâsîn suresi Duhân suresi
fetih suresi Hucurât suresi Kâf suresi
Necm suresi Rahmân suresi vakıa suresi
Haşr suresi Mülk suresi Hâkka suresi
İnşikâk suresi Alâ suresi Gâşiye suresi

En ünlü okuyucuların sesiyle Müddessir Suresi indirin:

Surah Al-Muddaththir mp3: yüksek kalitede dinlemek ve indirmek için okuyucuyu seçerek
Müddessir Suresi Ahmed El Agamy
Ahmed El Agamy
Müddessir Suresi Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
Müddessir Suresi Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
Müddessir Suresi Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
Müddessir Suresi Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
Müddessir Suresi Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
Müddessir Suresi Ali Al Hudhaifi
Ali Al Hudhaifi
Müddessir Suresi Fares Abbad
Fares Abbad
Müddessir Suresi Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
Müddessir Suresi Muhammad Jibril
Muhammad Jibril
Müddessir Suresi Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
Müddessir Suresi Al Hosary
Al Hosary
Müddessir Suresi Al-afasi
Mishari Al-afasi
Müddessir Suresi Nasser Al Qatami
Nasser Al Qatami
Müddessir Suresi Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Saturday, May 18, 2024

Bizim için dua et, teşekkürler