ሱረቱ አን-ነጅም ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አን-ነጅምን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (62 አንቀጽ — مكية). አን-ነጅም ስሙ, አን-ነጅም ትርጉም, አን-ነጅም mp3, አን-ነጅም pdf.

ሱረቱ አን-ነጅምን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَالنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَىٰ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
وَمَا يَنطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
عَلَّمَهُ شَدِيدُ الْقُوَىٰ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
ذُو مِرَّةٍ فَاسْتَوَىٰ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
وَهُوَ بِالْأُفُقِ الْأَعْلَىٰ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
فَأَوْحَىٰ إِلَىٰ عَبْدِهِ مَا أَوْحَىٰ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
مَا كَذَبَ الْفُؤَادُ مَا رَأَىٰ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
أَفَتُمَارُونَهُ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
وَلَقَدْ رَآهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَىٰ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
عِندَهَا جَنَّةُ الْمَأْوَىٰ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
إِذْ يَغْشَى السِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
مَا زَاغَ الْبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ آيَاتِ رَبِّهِ الْكُبْرَىٰ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
أَفَرَأَيْتُمُ اللَّاتَ وَالْعُزَّىٰ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
وَمَنَاةَ الثَّالِثَةَ الْأُخْرَىٰ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
أَلَكُمُ الذَّكَرُ وَلَهُ الْأُنثَىٰ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡
إِنْ هِيَ إِلَّا أَسْمَاءٌ سَمَّيْتُمُوهَا أَنتُمْ وَآبَاؤُكُم مَّا أَنزَلَ اللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَانٍ ۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ وَمَا تَهْوَى الْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَاءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ الْهُدَىٰ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
أَمْ لِلْإِنسَانِ مَا تَمَنَّىٰ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
فَلِلَّهِ الْآخِرَةُ وَالْأُولَىٰ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِالْآخِرَةِ لَيُسَمُّونَ الْمَلَائِكَةَ تَسْمِيَةَ الْأُنثَىٰ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
وَمَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ ۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ ۖ وَإِنَّ الظَّنَّ لَا يُغْنِي مِنَ الْحَقِّ شَيْئًا ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
فَأَعْرِضْ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكْرِنَا وَلَمْ يُرِدْ إِلَّا الْحَيَاةَ الدُّنْيَا ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
ذَٰلِكَ مَبْلَغُهُم مِّنَ الْعِلْمِ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِ وَهُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اهْتَدَىٰ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
وَلِلَّهِ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ لِيَجْزِيَ الَّذِينَ أَسَاءُوا بِمَا عَمِلُوا وَيَجْزِيَ الَّذِينَ أَحْسَنُوا بِالْحُسْنَى ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡
الَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَائِرَ الْإِثْمِ وَالْفَوَاحِشَ إِلَّا اللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَاسِعُ الْمَغْفِرَةِ ۚ هُوَ أَعْلَمُ بِكُمْ إِذْ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَإِذْ أَنتُمْ أَجِنَّةٌ فِي بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ ۖ فَلَا تُزَكُّوا أَنفُسَكُمْ ۖ هُوَ أَعْلَمُ بِمَنِ اتَّقَىٰ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
أَفَرَأَيْتَ الَّذِي تَوَلَّىٰ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
وَأَعْطَىٰ قَلِيلًا وَأَكْدَىٰ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
أَعِندَهُ عِلْمُ الْغَيْبِ فَهُوَ يَرَىٰ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
أَمْ لَمْ يُنَبَّأْ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
وَإِبْرَاهِيمَ الَّذِي وَفَّىٰ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَانِ إِلَّا مَا سَعَىٰ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
وَأَنَّ سَعْيَهُ سَوْفَ يُرَىٰ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
ثُمَّ يُجْزَاهُ الْجَزَاءَ الْأَوْفَىٰ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ الْمُنتَهَىٰ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
وَأَنَّهُ هُوَ أَضْحَكَ وَأَبْكَىٰ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
وَأَنَّهُ هُوَ أَمَاتَ وَأَحْيَا ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
وَأَنَّهُ خَلَقَ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَىٰ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
مِن نُّطْفَةٍ إِذَا تُمْنَىٰ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
وَأَنَّ عَلَيْهِ النَّشْأَةَ الْأُخْرَىٰ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
وَأَنَّهُ هُوَ أَغْنَىٰ وَأَقْنَىٰ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
وَأَنَّهُ هُوَ رَبُّ الشِّعْرَىٰ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
وَأَنَّهُ أَهْلَكَ عَادًا الْأُولَىٰ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
وَثَمُودَ فَمَا أَبْقَىٰ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
وَقَوْمَ نُوحٍ مِّن قَبْلُ ۖ إِنَّهُمْ كَانُوا هُمْ أَظْلَمَ وَأَطْغَىٰ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
وَالْمُؤْتَفِكَةَ أَهْوَىٰ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
فَغَشَّاهَا مَا غَشَّىٰ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
هَٰذَا نَذِيرٌ مِّنَ النُّذُرِ الْأُولَىٰ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
أَزِفَتِ الْآزِفَةُ ۝٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 57
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
لَيْسَ لَهَا مِن دُونِ اللَّهِ كَاشِفَةٌ ۝٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 58
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
أَفَمِنْ هَٰذَا الْحَدِيثِ تَعْجَبُونَ ۝٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 59
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
وَتَضْحَكُونَ وَلَا تَبْكُونَ ۝٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 60
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
وَأَنتُمْ سَامِدُونَ ۝٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 61
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
فَاسْجُدُوا لِلَّهِ وَاعْبُدُوا ۩ ۝٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 62
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡
← 52 አን-ነጅም (53/114) 54 →
ማንበብ ሱረቱ አን-ነጅም አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

53النجم An-Najm 📚 62 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አን-ነጅም — 62 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers