ሱረቱ አሽ-ሹዐራ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አሽ-ሹዐራ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አሽ-ሹዐራ ትርጉም. ሱረቱ አሽ-ሹዐራ (Meccan) 227 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አሽ-ሹዐራ

ﭑﭒ
26:1
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
ﭓﭔﭕﭖﭗ
26:2
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
26:3
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
26:4
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
26:5
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
26:6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
26:7
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
26:8
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
26:9
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
26:10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
26:11
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
26:12
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
ﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
26:13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
26:14
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
26:15
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
26:16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
26:17
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
26:18
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
26:19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
26:20
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
26:21
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
26:22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
26:23
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽ
26:24
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
ﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
26:25
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
26:26
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
26:27
(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
26:28
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
26:29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
26:30
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
26:31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
26:32
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
26:33
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
26:34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
26:35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
26:36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
ﯼﯽﯾﯿﰀ
26:37
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆ
26:38
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
ﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
26:39
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
26:40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
26:41
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
26:42
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
26:43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
26:44
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
26:45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
ﮈﮉﮊﮋ
26:46
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐ
26:47
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
ﮑﮒﮓﮔ
26:48
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
26:49
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
26:50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
26:51
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
26:52
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
26:53
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
ﯳﯴﯵﯶﯷ
26:54
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
ﯸﯹﯺﯻ
26:55
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
ﯼﯽﯾﯿ
26:56
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
ﰀﰁﰂﰃﰄ
26:57
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
ﰅﰆﰇﰈ
26:58
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
ﰉﰊﰋﰌﰍﰎ
26:59
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
ﰏﰐﰑ
26:60
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙ
26:61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
26:62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
26:63
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
ﭱﭲﭳﭴ
26:64
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
26:65
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
ﭻﭼﭽﭾ
26:66
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
26:67
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
26:68
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓ
26:69
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
26:70
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡ
26:71
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
26:72
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
ﮨﮩﮪﮫﮬ
26:73
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
26:74
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
26:75
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
ﯛﯜﯝﯞ
26:76
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
26:77
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
26:78
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯ
26:79
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴ
26:80
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
26:81
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
26:82
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
26:83
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
26:84
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
26:85
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
26:86
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
26:87
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
26:88
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷ
26:89
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
ﭸﭹﭺﭻ
26:90
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
ﭼﭽﭾﭿ
26:91
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
26:92
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
26:93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
ﮏﮐﮑﮒﮓ
26:94
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
ﮔﮕﮖﮗ
26:95
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜ
26:96
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
26:97
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨ
26:98
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
26:99
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓ
26:100
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
ﯔﯕﯖﯗ
26:101
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
26:102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
26:103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
26:104
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴ
26:105
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼ
26:106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﯽﯾﯿﰀﰁ
26:107
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﰂﰃﰄﰅ
26:108
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒ
26:109
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﰓﰔﰕﰖ
26:110
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
ﰗﰘﰙﰚﰛﰜﰝ
26:111
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
26:112
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
26:113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥ
26:114
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
26:115
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
26:116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
26:117
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄ
26:118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
26:119
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐ
26:120
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
26:121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
26:122
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮡﮢﮣﮤ
26:123
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
26:124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﮭﮮﮯﮰﮱ
26:125
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﯓﯔﯕﯖ
26:126
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
26:127
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
26:128
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
ﯪﯫﯬﯭﯮ
26:129
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
ﯯﯰﯱﯲﯳ
26:130
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
ﯴﯵﯶﯷ
26:131
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
26:132
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
ﯾﯿﰀﰁ
26:133
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
ﰂﰃﰄ
26:134
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋ
26:135
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
ﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
26:136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
26:137
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ﭗﭘﭙﭚ
26:138
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
26:139
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
26:140
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﭮﭯﭰﭱ
26:141
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
ﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
26:142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﭺﭻﭼﭽﭾ
26:143
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﭿﮀﮁﮂ
26:144
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
26:145
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
26:146
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
ﮖﮗﮘﮙ
26:147
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞ
26:148
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
26:149
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
ﮥﮦﮧﮨ
26:150
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
26:151
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕ
26:152
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
26:153
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
26:154
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
26:155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹ
26:156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
ﯺﯻﯼﯽ
26:157
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
26:158
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﰋﰌﰍﰎﰏﰐ
26:159
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
26:160
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
26:161
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﭞﭟﭠﭡﭢ
26:162
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﭣﭤﭥﭦ
26:163
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
26:164
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﭴﭵﭶﭷﭸ
26:165
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
26:166
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
ﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
26:167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
26:168
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
26:169
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
ﮛﮜﮝﮞ
26:170
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣ
26:171
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
ﮤﮥﮦﮧ
26:172
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
26:173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
26:174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
26:175
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥ
26:176
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
26:177
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﯭﯮﯯﯰﯱ
26:178
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﯲﯳﯴﯵ
26:179
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
26:180
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
26:181
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
ﰋﰌﰍﰎ
26:182
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
ﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗﰘ
26:183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
26:184
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
ﭗﭘﭙﭚﭛﭜ
26:185
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
ﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
26:186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
26:187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
26:188
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
26:189
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
26:190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
26:191
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗ
26:192
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜ
26:193
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
26:194
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
ﮣﮤﮥﮦ
26:195
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫ
26:196
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
26:197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
26:198
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
26:199
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
26:200
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
26:201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
26:202
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼ
26:203
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
ﯽﯾﯿ
26:204
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
ﰀﰁﰂﰃﰄ
26:205
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
26:206
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
26:207
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟ
26:208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
ﭠﭡﭢﭣﭤ
26:209
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
26:210
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
26:211
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
ﭰﭱﭲﭳﭴ
26:212
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
26:213
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
ﭿﮀﮁﮂ
26:214
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
26:215
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
26:216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖ
26:217
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛ
26:218
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
ﮜﮝﮞﮟ
26:219
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
ﮠﮡﮢﮣﮤ
26:220
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
26:221
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
26:222
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
ﯓﯔﯕﯖﯗ
26:223
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
ﯘﯙﯚﯛ
26:224
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
26:225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
26:226
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
26:227
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







