ሱረቱ አሽ-ሹዐራ
PDF —
Built right in your browser — download starts automatically
ሱረቱ አሽ-ሹዐራ pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አሽ-ሹዐራ pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አሽ-ሹዐራ ትርጉም. አሽ-ሹዐራ (Meccan) 227 አንቀጽ.
Related
- አሽ-ሹዐራ ትርጉምአማርኛ
- አሽ-ሹዐራ mp3ስሙ
- Quran Index አማርኛ114
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አሽ-ሹዐራ

ﭑﭒ
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
ﭓﭔﭕﭖﭗ
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞ
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
ﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚﮛ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
ﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
ﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽ
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
ﭾﭿﮀﮁﮂﮃ
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
ﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪ
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
ﯼﯽﯾﯿﰀ
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆ
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
ﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘ
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
ﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
ﮈﮉﮊﮋ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐ
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
ﮑﮒﮓﮔ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
ﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
ﯳﯴﯵﯶﯷ
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
ﯸﯹﯺﯻ
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
ﯼﯽﯾﯿ
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
ﰀﰁﰂﰃﰄ
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
ﰅﰆﰇﰈ
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
ﰉﰊﰋﰌﰍﰎ
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
ﰏﰐﰑ
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗﭘﭙ
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
ﭢﭣﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
ﭱﭲﭳﭴ
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
ﭻﭼﭽﭾ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮏﮐﮑﮒﮓ
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠﮡ
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦﮧ
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
ﮨﮩﮪﮫﮬ
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
ﯛﯜﯝﯞ
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
ﯫﯬﯭﯮﯯ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤ
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
ﭸﭹﭺﭻ
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
ﭼﭽﭾﭿ
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
ﮏﮐﮑﮒﮓ
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
ﮔﮕﮖﮗ
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜ
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨ
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓ
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
ﯔﯕﯖﯗ
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﯰﯱﯲﯳﯴ
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼ
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﯽﯾﯿﰀﰁ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﰂﰃﰄﰅ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﰓﰔﰕﰖ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
ﰗﰘﰙﰚﰛﰜﰝ
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥ
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄ
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋ
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐ
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮡﮢﮣﮤ
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﮭﮮﮯﮰﮱ
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﯓﯔﯕﯖ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
ﯪﯫﯬﯭﯮ
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
ﯯﯰﯱﯲﯳ
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
ﯴﯵﯶﯷ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
ﯾﯿﰀﰁ
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
ﰂﰃﰄ
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋ
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
ﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ﭗﭘﭙﭚ
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﭮﭯﭰﭱ
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
ﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﭺﭻﭼﭽﭾ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﭿﮀﮁﮂ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
ﮖﮗﮘﮙ
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞ
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
ﮟﮠﮡﮢﮣﮤ
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
ﮥﮦﮧﮨ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﮩﮪﮫﮬﮭ
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕ
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹ
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
ﯺﯻﯼﯽ
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﰋﰌﰍﰎﰏﰐ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﭞﭟﭠﭡﭢ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﭣﭤﭥﭦ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﭴﭵﭶﭷﭸ
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
ﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
ﮛﮜﮝﮞ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣ
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
ﮤﮥﮦﮧ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭﮮﮯ
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
ﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥ
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
ﯭﯮﯯﯰﯱ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
ﯲﯳﯴﯵ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂ
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
ﰋﰌﰍﰎ
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
ﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕﰖﰗﰘ
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
ﭗﭘﭙﭚﭛﭜ
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
ﭝﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯﭰ
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
ﮓﮔﮕﮖﮗ
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜ
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
ﮣﮤﮥﮦ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫ
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
ﯗﯘﯙﯚﯛﯜ
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
ﯲﯳﯴﯵﯶﯷ
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
ﯸﯹﯺﯻﯼ
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
ﯽﯾﯿ
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
ﰀﰁﰂﰃﰄ
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖﭗ
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝﭞﭟ
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
ﭠﭡﭢﭣﭤ
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
ﭥﭦﭧﭨﭩ
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
ﭰﭱﭲﭳﭴ
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
ﭿﮀﮁﮂ
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉ
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖ
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛ
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
ﮜﮝﮞﮟ
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
ﮠﮡﮢﮣﮤ
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
ﯓﯔﯕﯖﯗ
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
ﯘﯙﯚﯛ
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Tuesday, August 18, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







