ሱረቱ አሽ-ሹዐራ ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አሽ-ሹዐራን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (227 አንቀጽ — مكية). አሽ-ሹዐራ ስሙ, አሽ-ሹዐራ ትርጉም, አሽ-ሹዐራ mp3, አሽ-ሹዐራ pdf.

ሱረቱ አሽ-ሹዐራን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
طسم ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ الْمُبِينِ ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
لَعَلَّكَ بَاخِعٌ نَّفْسَكَ أَلَّا يَكُونُوا مُؤْمِنِينَ ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
إِن نَّشَأْ نُنَزِّلْ عَلَيْهِم مِّنَ السَّمَاءِ آيَةً فَظَلَّتْ أَعْنَاقُهُمْ لَهَا خَاضِعِينَ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
وَمَا يَأْتِيهِم مِّن ذِكْرٍ مِّنَ الرَّحْمَٰنِ مُحْدَثٍ إِلَّا كَانُوا عَنْهُ مُعْرِضِينَ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
فَقَدْ كَذَّبُوا فَسَيَأْتِيهِمْ أَنبَاءُ مَا كَانُوا بِهِ يَسْتَهْزِئُونَ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
أَوَلَمْ يَرَوْا إِلَى الْأَرْضِ كَمْ أَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوْجٍ كَرِيمٍ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
وَإِذْ نَادَىٰ رَبُّكَ مُوسَىٰ أَنِ ائْتِ الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
قَوْمَ فِرْعَوْنَ ۚ أَلَا يَتَّقُونَ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
قَالَ رَبِّ إِنِّي أَخَافُ أَن يُكَذِّبُونِ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
وَيَضِيقُ صَدْرِي وَلَا يَنطَلِقُ لِسَانِي فَأَرْسِلْ إِلَىٰ هَارُونَ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
وَلَهُمْ عَلَيَّ ذَنبٌ فَأَخَافُ أَن يَقْتُلُونِ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
قَالَ كَلَّا ۖ فَاذْهَبَا بِآيَاتِنَا ۖ إِنَّا مَعَكُم مُّسْتَمِعُونَ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
فَأْتِيَا فِرْعَوْنَ فَقُولَا إِنَّا رَسُولُ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
أَنْ أَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
قَالَ أَلَمْ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدًا وَلَبِثْتَ فِينَا مِنْ عُمُرِكَ سِنِينَ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
وَفَعَلْتَ فَعْلَتَكَ الَّتِي فَعَلْتَ وَأَنتَ مِنَ الْكَافِرِينَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
قَالَ فَعَلْتُهَا إِذًا وَأَنَا مِنَ الضَّالِّينَ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
فَفَرَرْتُ مِنكُمْ لَمَّا خِفْتُكُمْ فَوَهَبَ لِي رَبِّي حُكْمًا وَجَعَلَنِي مِنَ الْمُرْسَلِينَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
وَتِلْكَ نِعْمَةٌ تَمُنُّهَا عَلَيَّ أَنْ عَبَّدتَّ بَنِي إِسْرَائِيلَ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
قَالَ فِرْعَوْنُ وَمَا رَبُّ الْعَالَمِينَ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
قَالَ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
قَالَ لِمَنْ حَوْلَهُ أَلَا تَسْتَمِعُونَ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
قَالَ رَبُّكُمْ وَرَبُّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
قَالَ إِنَّ رَسُولَكُمُ الَّذِي أُرْسِلَ إِلَيْكُمْ لَمَجْنُونٌ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡
قَالَ رَبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَمَا بَيْنَهُمَا ۖ إِن كُنتُمْ تَعْقِلُونَ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
قَالَ لَئِنِ اتَّخَذْتَ إِلَٰهًا غَيْرِي لَأَجْعَلَنَّكَ مِنَ الْمَسْجُونِينَ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
قَالَ أَوَلَوْ جِئْتُكَ بِشَيْءٍ مُّبِينٍ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
قَالَ فَأْتِ بِهِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
فَأَلْقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعْبَانٌ مُّبِينٌ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
وَنَزَعَ يَدَهُ فَإِذَا هِيَ بَيْضَاءُ لِلنَّاظِرِينَ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
قَالَ لِلْمَلَإِ حَوْلَهُ إِنَّ هَٰذَا لَسَاحِرٌ عَلِيمٌ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
يُرِيدُ أَن يُخْرِجَكُم مِّنْ أَرْضِكُم بِسِحْرِهِ فَمَاذَا تَأْمُرُونَ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
قَالُوا أَرْجِهْ وَأَخَاهُ وَابْعَثْ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
يَأْتُوكَ بِكُلِّ سَحَّارٍ عَلِيمٍ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
فَجُمِعَ السَّحَرَةُ لِمِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
وَقِيلَ لِلنَّاسِ هَلْ أَنتُم مُّجْتَمِعُونَ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
لَعَلَّنَا نَتَّبِعُ السَّحَرَةَ إِن كَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
فَلَمَّا جَاءَ السَّحَرَةُ قَالُوا لِفِرْعَوْنَ أَئِنَّ لَنَا لَأَجْرًا إِن كُنَّا نَحْنُ الْغَالِبِينَ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
قَالَ نَعَمْ وَإِنَّكُمْ إِذًا لَّمِنَ الْمُقَرَّبِينَ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
قَالَ لَهُم مُّوسَىٰ أَلْقُوا مَا أَنتُم مُّلْقُونَ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
فَأَلْقَوْا حِبَالَهُمْ وَعِصِيَّهُمْ وَقَالُوا بِعِزَّةِ فِرْعَوْنَ إِنَّا لَنَحْنُ الْغَالِبُونَ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
فَأَلْقَىٰ مُوسَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ تَلْقَفُ مَا يَأْفِكُونَ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
فَأُلْقِيَ السَّحَرَةُ سَاجِدِينَ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ الْعَالَمِينَ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَارُونَ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
قَالَ آمَنتُمْ لَهُ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّهُ لَكَبِيرُكُمُ الَّذِي عَلَّمَكُمُ السِّحْرَ فَلَسَوْفَ تَعْلَمُونَ ۚ لَأُقَطِّعَنَّ أَيْدِيَكُمْ وَأَرْجُلَكُم مِّنْ خِلَافٍ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمْ أَجْمَعِينَ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
قَالُوا لَا ضَيْرَ ۖ إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا مُنقَلِبُونَ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
إِنَّا نَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لَنَا رَبُّنَا خَطَايَانَا أَن كُنَّا أَوَّلَ الْمُؤْمِنِينَ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
۞ وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنْ أَسْرِ بِعِبَادِي إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
فَأَرْسَلَ فِرْعَوْنُ فِي الْمَدَائِنِ حَاشِرِينَ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
إِنَّ هَٰؤُلَاءِ لَشِرْذِمَةٌ قَلِيلُونَ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
وَإِنَّهُمْ لَنَا لَغَائِظُونَ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَاذِرُونَ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
فَأَخْرَجْنَاهُم مِّن جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ۝٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 57
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
وَكُنُوزٍ وَمَقَامٍ كَرِيمٍ ۝٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 58
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
كَذَٰلِكَ وَأَوْرَثْنَاهَا بَنِي إِسْرَائِيلَ ۝٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 59
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
فَأَتْبَعُوهُم مُّشْرِقِينَ ۝٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 60
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
فَلَمَّا تَرَاءَى الْجَمْعَانِ قَالَ أَصْحَابُ مُوسَىٰ إِنَّا لَمُدْرَكُونَ ۝٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
قَالَ كَلَّا ۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ ۝٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
فَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنِ اضْرِب بِّعَصَاكَ الْبَحْرَ ۖ فَانفَلَقَ فَكَانَ كُلُّ فِرْقٍ كَالطَّوْدِ الْعَظِيمِ ۝٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 63
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
وَأَزْلَفْنَا ثَمَّ الْآخَرِينَ ۝٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 64
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
وَأَنجَيْنَا مُوسَىٰ وَمَن مَّعَهُ أَجْمَعِينَ ۝٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 65
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ ۝٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 66
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 67
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 68
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ إِبْرَاهِيمَ ۝٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 69
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَا تَعْبُدُونَ ۝٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 70
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
قَالُوا نَعْبُدُ أَصْنَامًا فَنَظَلُّ لَهَا عَاكِفِينَ ۝٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 71
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
قَالَ هَلْ يَسْمَعُونَكُمْ إِذْ تَدْعُونَ ۝٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 72
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
أَوْ يَنفَعُونَكُمْ أَوْ يَضُرُّونَ ۝٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 73
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
قَالُوا بَلْ وَجَدْنَا آبَاءَنَا كَذَٰلِكَ يَفْعَلُونَ ۝٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 74
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
قَالَ أَفَرَأَيْتُم مَّا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ ۝٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 75
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
أَنتُمْ وَآبَاؤُكُمُ الْأَقْدَمُونَ ۝٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 76
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
فَإِنَّهُمْ عَدُوٌّ لِّي إِلَّا رَبَّ الْعَالَمِينَ ۝٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 77
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
الَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهْدِينِ ۝٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 78
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
وَالَّذِي هُوَ يُطْعِمُنِي وَيَسْقِينِ ۝٧٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 79
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
وَإِذَا مَرِضْتُ فَهُوَ يَشْفِينِ ۝٨٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 80
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ ۝٨١
📖 ትርጉም አንቀጽ 81
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
وَالَّذِي أَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لِي خَطِيئَتِي يَوْمَ الدِّينِ ۝٨٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 82
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
رَبِّ هَبْ لِي حُكْمًا وَأَلْحِقْنِي بِالصَّالِحِينَ ۝٨٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 83
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
وَاجْعَل لِّي لِسَانَ صِدْقٍ فِي الْآخِرِينَ ۝٨٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 84
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
وَاجْعَلْنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ النَّعِيمِ ۝٨٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 85
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
وَاغْفِرْ لِأَبِي إِنَّهُ كَانَ مِنَ الضَّالِّينَ ۝٨٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 86
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
وَلَا تُخْزِنِي يَوْمَ يُبْعَثُونَ ۝٨٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 87
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ ۝٨٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 88
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ ۝٨٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 89
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
وَأُزْلِفَتِ الْجَنَّةُ لِلْمُتَّقِينَ ۝٩٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 90
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِلْغَاوِينَ ۝٩١
📖 ትርጉም አንቀጽ 91
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
وَقِيلَ لَهُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ تَعْبُدُونَ ۝٩٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 92
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
مِن دُونِ اللَّهِ هَلْ يَنصُرُونَكُمْ أَوْ يَنتَصِرُونَ ۝٩٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
فَكُبْكِبُوا فِيهَا هُمْ وَالْغَاوُونَ ۝٩٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 94
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
وَجُنُودُ إِبْلِيسَ أَجْمَعُونَ ۝٩٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 95
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
قَالُوا وَهُمْ فِيهَا يَخْتَصِمُونَ ۝٩٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 96
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
تَاللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَالٍ مُّبِينٍ ۝٩٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 97
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
إِذْ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ ۝٩٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 98
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
وَمَا أَضَلَّنَا إِلَّا الْمُجْرِمُونَ ۝٩٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 99
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
فَمَا لَنَا مِن شَافِعِينَ ۝١٠٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 100
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٍ ۝١٠١
📖 ትርጉም አንቀጽ 101
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
فَلَوْ أَنَّ لَنَا كَرَّةً فَنَكُونَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ۝١٠٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٠٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٠٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 104
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
كَذَّبَتْ قَوْمُ نُوحٍ الْمُرْسَلِينَ ۝١٠٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 105
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٠٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ۝١٠٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 107
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٠٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 108
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٠٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 109
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 110
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
۞ قَالُوا أَنُؤْمِنُ لَكَ وَاتَّبَعَكَ الْأَرْذَلُونَ ۝١١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 111
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
قَالَ وَمَا عِلْمِي بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ ۝١١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 112
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
إِنْ حِسَابُهُمْ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّي ۖ لَوْ تَشْعُرُونَ ۝١١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
وَمَا أَنَا بِطَارِدِ الْمُؤْمِنِينَ ۝١١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 114
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ مُّبِينٌ ۝١١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 115
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا نُوحُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمَرْجُومِينَ ۝١١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
قَالَ رَبِّ إِنَّ قَوْمِي كَذَّبُونِ ۝١١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 117
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
فَافْتَحْ بَيْنِي وَبَيْنَهُمْ فَتْحًا وَنَجِّنِي وَمَن مَّعِيَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ۝١١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
فَأَنجَيْنَاهُ وَمَن مَّعَهُ فِي الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ ۝١١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 119
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
ثُمَّ أَغْرَقْنَا بَعْدُ الْبَاقِينَ ۝١٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 120
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 122
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
كَذَّبَتْ عَادٌ الْمُرْسَلِينَ ۝١٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 123
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ هُودٌ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ۝١٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 125
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 126
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 127
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
أَتَبْنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ آيَةً تَعْبَثُونَ ۝١٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 128
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمْ تَخْلُدُونَ ۝١٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 129
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
وَإِذَا بَطَشْتُم بَطَشْتُمْ جَبَّارِينَ ۝١٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 130
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 131
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
وَاتَّقُوا الَّذِي أَمَدَّكُم بِمَا تَعْلَمُونَ ۝١٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 132
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
أَمَدَّكُم بِأَنْعَامٍ وَبَنِينَ ۝١٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 133
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
وَجَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ۝١٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 134
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ ۝١٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 135
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
قَالُوا سَوَاءٌ عَلَيْنَا أَوَعَظْتَ أَمْ لَمْ تَكُن مِّنَ الْوَاعِظِينَ ۝١٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
إِنْ هَٰذَا إِلَّا خُلُقُ الْأَوَّلِينَ ۝١٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 137
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ ۝١٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 138
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
فَكَذَّبُوهُ فَأَهْلَكْنَاهُمْ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 139
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 140
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
كَذَّبَتْ ثَمُودُ الْمُرْسَلِينَ ۝١٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 141
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ صَالِحٌ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ۝١٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 143
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 144
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 145
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
أَتُتْرَكُونَ فِي مَا هَاهُنَا آمِنِينَ ۝١٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 146
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
فِي جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ ۝١٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 147
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
وَزُرُوعٍ وَنَخْلٍ طَلْعُهَا هَضِيمٌ ۝١٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 148
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
وَتَنْحِتُونَ مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا فَارِهِينَ ۝١٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 149
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 150
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
وَلَا تُطِيعُوا أَمْرَ الْمُسْرِفِينَ ۝١٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 151
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
الَّذِينَ يُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ وَلَا يُصْلِحُونَ ۝١٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 152
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ ۝١٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 153
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
مَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا فَأْتِ بِآيَةٍ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ۝١٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 154
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
قَالَ هَٰذِهِ نَاقَةٌ لَّهَا شِرْبٌ وَلَكُمْ شِرْبُ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ ۝١٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوءٍ فَيَأْخُذَكُمْ عَذَابُ يَوْمٍ عَظِيمٍ ۝١٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
فَعَقَرُوهَا فَأَصْبَحُوا نَادِمِينَ ۝١٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 157
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
فَأَخَذَهُمُ الْعَذَابُ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 158
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 159
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
كَذَّبَتْ قَوْمُ لُوطٍ الْمُرْسَلِينَ ۝١٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 160
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 161
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ۝١٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 162
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 163
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 164
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
أَتَأْتُونَ الذُّكْرَانَ مِنَ الْعَالَمِينَ ۝١٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 165
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمْ رَبُّكُم مِّنْ أَزْوَاجِكُم ۚ بَلْ أَنتُمْ قَوْمٌ عَادُونَ ۝١٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 166
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
قَالُوا لَئِن لَّمْ تَنتَهِ يَا لُوطُ لَتَكُونَنَّ مِنَ الْمُخْرَجِينَ ۝١٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
قَالَ إِنِّي لِعَمَلِكُم مِّنَ الْقَالِينَ ۝١٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 168
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
رَبِّ نَجِّنِي وَأَهْلِي مِمَّا يَعْمَلُونَ ۝١٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 169
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
فَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ ۝١٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 170
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ ۝١٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 171
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ ۝١٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 172
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ ۝١٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 175
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
كَذَّبَ أَصْحَابُ الْأَيْكَةِ الْمُرْسَلِينَ ۝١٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 176
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
إِذْ قَالَ لَهُمْ شُعَيْبٌ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 177
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
إِنِّي لَكُمْ رَسُولٌ أَمِينٌ ۝١٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 178
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
فَاتَّقُوا اللَّهَ وَأَطِيعُونِ ۝١٧٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 179
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
وَمَا أَسْأَلُكُمْ عَلَيْهِ مِنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٨٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 180
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
۞ أَوْفُوا الْكَيْلَ وَلَا تَكُونُوا مِنَ الْمُخْسِرِينَ ۝١٨١
📖 ትርጉም አንቀጽ 181
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
وَزِنُوا بِالْقِسْطَاسِ الْمُسْتَقِيمِ ۝١٨٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 182
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
وَلَا تَبْخَسُوا النَّاسَ أَشْيَاءَهُمْ وَلَا تَعْثَوْا فِي الْأَرْضِ مُفْسِدِينَ ۝١٨٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
وَاتَّقُوا الَّذِي خَلَقَكُمْ وَالْجِبِلَّةَ الْأَوَّلِينَ ۝١٨٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 184
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
قَالُوا إِنَّمَا أَنتَ مِنَ الْمُسَحَّرِينَ ۝١٨٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 185
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
وَمَا أَنتَ إِلَّا بَشَرٌ مِّثْلُنَا وَإِن نَّظُنُّكَ لَمِنَ الْكَاذِبِينَ ۝١٨٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
فَأَسْقِطْ عَلَيْنَا كِسَفًا مِّنَ السَّمَاءِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ ۝١٨٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
قَالَ رَبِّي أَعْلَمُ بِمَا تَعْمَلُونَ ۝١٨٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 188
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَهُمْ عَذَابُ يَوْمِ الظُّلَّةِ ۚ إِنَّهُ كَانَ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ ۝١٨٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 189
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً ۖ وَمَا كَانَ أَكْثَرُهُم مُّؤْمِنِينَ ۝١٩٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ الْعَزِيزُ الرَّحِيمُ ۝١٩١
📖 ትርጉም አንቀጽ 191
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
وَإِنَّهُ لَتَنزِيلُ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٩٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 192
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
نَزَلَ بِهِ الرُّوحُ الْأَمِينُ ۝١٩٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 193
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
عَلَىٰ قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنذِرِينَ ۝١٩٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 194
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
بِلِسَانٍ عَرَبِيٍّ مُّبِينٍ ۝١٩٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 195
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
وَإِنَّهُ لَفِي زُبُرِ الْأَوَّلِينَ ۝١٩٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 196
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
أَوَلَمْ يَكُن لَّهُمْ آيَةً أَن يَعْلَمَهُ عُلَمَاءُ بَنِي إِسْرَائِيلَ ۝١٩٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
وَلَوْ نَزَّلْنَاهُ عَلَىٰ بَعْضِ الْأَعْجَمِينَ ۝١٩٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 198
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
فَقَرَأَهُ عَلَيْهِم مَّا كَانُوا بِهِ مُؤْمِنِينَ ۝١٩٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 199
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
كَذَٰلِكَ سَلَكْنَاهُ فِي قُلُوبِ الْمُجْرِمِينَ ۝٢٠٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 200
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
لَا يُؤْمِنُونَ بِهِ حَتَّىٰ يَرَوُا الْعَذَابَ الْأَلِيمَ ۝٢٠١
📖 ትርጉም አንቀጽ 201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
فَيَأْتِيَهُم بَغْتَةً وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ ۝٢٠٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 202
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
فَيَقُولُوا هَلْ نَحْنُ مُنظَرُونَ ۝٢٠٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 203
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ ۝٢٠٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 204
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
أَفَرَأَيْتَ إِن مَّتَّعْنَاهُمْ سِنِينَ ۝٢٠٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 205
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
ثُمَّ جَاءَهُم مَّا كَانُوا يُوعَدُونَ ۝٢٠٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 206
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
مَا أَغْنَىٰ عَنْهُم مَّا كَانُوا يُمَتَّعُونَ ۝٢٠٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 207
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
وَمَا أَهْلَكْنَا مِن قَرْيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ ۝٢٠٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
ذِكْرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَالِمِينَ ۝٢٠٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 209
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
وَمَا تَنَزَّلَتْ بِهِ الشَّيَاطِينُ ۝٢١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 210
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
وَمَا يَنبَغِي لَهُمْ وَمَا يَسْتَطِيعُونَ ۝٢١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 211
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
إِنَّهُمْ عَنِ السَّمْعِ لَمَعْزُولُونَ ۝٢١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 212
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
فَلَا تَدْعُ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ فَتَكُونَ مِنَ الْمُعَذَّبِينَ ۝٢١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 213
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
وَأَنذِرْ عَشِيرَتَكَ الْأَقْرَبِينَ ۝٢١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 214
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِمَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ ۝٢١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 215
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
فَإِنْ عَصَوْكَ فَقُلْ إِنِّي بَرِيءٌ مِّمَّا تَعْمَلُونَ ۝٢١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
وَتَوَكَّلْ عَلَى الْعَزِيزِ الرَّحِيمِ ۝٢١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 217
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
الَّذِي يَرَاكَ حِينَ تَقُومُ ۝٢١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 218
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
وَتَقَلُّبَكَ فِي السَّاجِدِينَ ۝٢١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 219
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ ۝٢٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 220
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
هَلْ أُنَبِّئُكُمْ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ الشَّيَاطِينُ ۝٢٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 221
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٍ ۝٢٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 222
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
يُلْقُونَ السَّمْعَ وَأَكْثَرُهُمْ كَاذِبُونَ ۝٢٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 223
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
وَالشُّعَرَاءُ يَتَّبِعُهُمُ الْغَاوُونَ ۝٢٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 224
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
أَلَمْ تَرَ أَنَّهُمْ فِي كُلِّ وَادٍ يَهِيمُونَ ۝٢٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
وَأَنَّهُمْ يَقُولُونَ مَا لَا يَفْعَلُونَ ۝٢٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 226
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَذَكَرُوا اللَّهَ كَثِيرًا وَانتَصَرُوا مِن بَعْدِ مَا ظُلِمُوا ۗ وَسَيَعْلَمُ الَّذِينَ ظَلَمُوا أَيَّ مُنقَلَبٍ يَنقَلِبُونَ ۝٢٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 227
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
← 25 አሽ-ሹዐራ (26/114) 27 →
ማንበብ ሱረቱ አሽ-ሹዐራ አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

26الشعراء Ash-Shu'ara 📚 227 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አሽ-ሹዐራ — 227 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers