ሱረቱ አስ-ሳፋት pdf — አውርድ (አማርኛ)
ሱረቱ አስ-ሳፋት pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አስ-ሳፋት ትርጉም. ሱረቱ አስ-ሳፋት (Meccan) 182 አንቀጽ.
Related
More ሱረቱ PDF
ሱረቱ አስ-ሳፋት

ﭑﭒﭓ
37:1
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
ﭔﭕﭖ
37:2
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
ﭗﭘﭙ
37:3
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
ﭚﭛﭜﭝ
37:4
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
37:5
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
37:6
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
37:7
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
37:8
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
37:9
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
37:10
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
37:11
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
ﮙﮚﮛﮜ
37:12
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
37:13
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦ
37:14
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
37:15
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
37:16
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
ﯗﯘﯙ
37:17
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
37:18
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
37:19
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
37:20
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
37:21
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
37:22
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
37:23
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊ
37:24
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
37:25
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚ
37:26
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
37:27
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
37:28
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
37:29
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
37:30
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
37:31
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆ
37:32
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
37:33
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑ
37:34
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
37:35
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
37:36
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
37:37
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮ
37:38
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
37:39
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛ
37:40
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠ
37:41
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
ﯡﯢﯣﯤ
37:42
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
ﯥﯦﯧﯨ
37:43
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
ﯩﯪﯫﯬ
37:44
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
37:45
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
ﯳﯴﯵﯶ
37:46
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
37:47
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
ﯿﰀﰁﰂﰃ
37:48
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
ﰄﰅﰆﰇ
37:49
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
ﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
37:50
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
37:51
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
37:52
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
37:53
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢ
37:54
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
37:55
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
37:56
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
37:57
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
ﭶﭷﭸﭹ
37:58
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
37:59
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
37:60
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋ
37:61
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
37:62
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
ﮓﮔﮕﮖﮗ
37:63
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
37:64
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣ
37:65
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
37:66
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
37:67
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙ
37:68
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
37:69
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣ
37:70
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
37:71
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮ
37:72
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
37:73
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
37:74
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿ
37:75
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
ﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
37:76
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
37:77
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
ﭖﭗﭘﭙﭚ
37:78
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
37:79
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
ﭡﭢﭣﭤﭥ
37:80
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪ
37:81
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
ﭫﭬﭭﭮ
37:82
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
37:83
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
37:84
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
37:85
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
37:86
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
ﮈﮉﮊﮋﮌ
37:87
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑ
37:88
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
ﮒﮓﮔﮕ
37:89
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
ﮖﮗﮘﮙ
37:90
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
37:91
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
ﮡﮢﮣﮤﮥ
37:92
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
ﮦﮧﮨﮩﮪ
37:93
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
ﮫﮬﮭﮮ
37:94
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔ
37:95
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
ﯕﯖﯗﯘﯙ
37:96
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
ﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
37:97
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
ﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
37:98
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮ
37:99
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
37:100
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
ﯵﯶﯷﯸ
37:101
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
ﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
37:102
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
37:103
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
ﭖﭗﭘﭙ
37:104
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
37:105
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
37:106
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
ﭩﭪﭫﭬ
37:107
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱ
37:108
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
ﭲﭳﭴﭵ
37:109
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
ﭶﭷﭸﭹ
37:110
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾ
37:111
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄ
37:112
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
37:113
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
37:114
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
37:115
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
37:116
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
ﮢﮣﮤﮥ
37:117
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
ﮦﮧﮨﮩ
37:118
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮ
37:119
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔ
37:120
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙ
37:121
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
37:122
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣ
37:123
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
37:124
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
37:125
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
37:126
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
ﭑﭒﭓﭔ
37:127
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
ﭕﭖﭗﭘﭙ
37:128
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞ
37:129
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣ
37:130
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨ
37:131
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭ
37:132
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲ
37:133
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷ
37:134
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﭸﭹﭺﭻﭼ
37:135
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
ﭽﭾﭿﮀ
37:136
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅ
37:137
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
ﮆﮇﮈﮉﮊ
37:138
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
ﮋﮌﮍﮎﮏ
37:139
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
37:140
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚ
37:141
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟ
37:142
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
ﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
37:143
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
37:144
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
37:145
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙ
37:146
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
37:147
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥ
37:148
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
37:149
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
37:150
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
ﯳﯴﯵﯶﯷﯸ
37:151
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
ﯹﯺﯻﯼﯽ
37:152
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂ
37:153
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
ﭑﭒﭓﭔﭕ
37:154
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
ﭖﭗﭘ
37:155
አትገነዘቡምን?
ﭙﭚﭛﭜﭝ
37:156
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
37:157
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
37:158
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
ﭰﭱﭲﭳﭴ
37:159
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹ
37:160
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
ﭺﭻﭼﭽ
37:161
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
ﭾﭿﮀﮁﮂ
37:162
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
37:163
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
37:164
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
ﮐﮑﮒﮓ
37:165
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
ﮔﮕﮖﮗ
37:166
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
ﮘﮙﮚﮛ
37:167
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
37:168
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
ﮣﮤﮥﮦﮧ
37:169
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
37:170
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
37:171
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
ﯕﯖﯗﯘ
37:172
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝ
37:173
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢ
37:174
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
ﯣﯤﯥﯦ
37:175
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
ﯧﯨﯩ
37:176
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
37:177
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
ﯱﯲﯳﯴﯵ
37:178
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
ﯶﯷﯸﯹ
37:179
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
37:180
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
ﰁﰂﰃﰄ
37:181
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
ﰅﰆﰇﰈﰉ
37:182
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
ቅዱስ ቁርኣን
Wednesday, September 9, 2026
Don't forget us in your sincere prayers







