ሱረቱ አስ-ሳፋት
PDF —
182 አንቀጽ Meccan PDF
Built right in your browser — download starts automatically

ሱረቱ አስ-ሳፋት pdf — አውርድ (አማርኛ)

ሱረቱ አስ-ሳፋት pdf አማርኛ — አውርድ ሱረቱ አስ-ሳፋት ትርጉም. አስ-ሳፋት (Meccan) 182 አንቀጽ.

← ያሲንአስ-ሳፋት ሳድ →


ሱረቱ አስ-ሳፋት
182 አንቀጽ · Meccan · አማርኛ
bismillah
ﭑﭒﭓ
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
ﭔﭕﭖ
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
ﭗﭘﭙ
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
ﭚﭛﭜﭝ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱﭲ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
ﭽﭾﭿﮀﮁﮂ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
ﮙﮚﮛﮜ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
ﮧﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
ﯗﯘﯙ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
ﰆﰇﰈﰉﰊ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦﭧ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
ﭨﭩﭪﭫﭬﭭ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵﭶﭷﭸﭹ
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
ﯜﯝﯞﯟﯠ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
ﯡﯢﯣﯤ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
ﯥﯦﯧﯨ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
ﯩﯪﯫﯬ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
ﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
ﯳﯴﯵﯶ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
ﯷﯸﯹﯺﯻﯼﯽﯾ
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
ﯿﰀﰁﰂﰃ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
ﰄﰅﰆﰇ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
ﰈﰉﰊﰋﰌﰍ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
ﭞﭟﭠﭡﭢ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
ﭶﭷﭸﭹ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅﮆ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
ﮇﮈﮉﮊﮋ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
ﮓﮔﮕﮖﮗ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝﮞ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
ﮟﮠﮡﮢﮣ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
ﯪﯫﯬﯭﯮ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
ﰀﰁﰂﰃﰄﰅ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
ﭖﭗﭘﭙﭚ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
ﭛﭜﭝﭞﭟﭠ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
ﭡﭢﭣﭤﭥ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭦﭧﭨﭩﭪ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
ﭫﭬﭭﭮ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
ﮈﮉﮊﮋﮌ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
ﮍﮎﮏﮐﮑ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
ﮒﮓﮔﮕ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
ﮖﮗﮘﮙ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
ﮡﮢﮣﮤﮥ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
ﮦﮧﮨﮩﮪ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
ﮫﮬﮭﮮ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
ﯕﯖﯗﯘﯙ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
ﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
ﯢﯣﯤﯥﯦﯧ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭﯮ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
ﯵﯶﯷﯸ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
ﯹﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀﰁﰂﰃﰄﰅﰆﰇﰈﰉﰊﰋﰌﰍﰎﰏﰐﰑﰒﰓﰔﰕ
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
ﭖﭗﭘﭙ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟﭠﭡﭢ
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
ﭩﭪﭫﭬ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
ﭭﭮﭯﭰﭱ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
ﭲﭳﭴﭵ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
ﭶﭷﭸﭹ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ﭺﭻﭼﭽﭾ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
ﭿﮀﮁﮂﮃﮄ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
ﮢﮣﮤﮥ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
ﮦﮧﮨﮩ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
ﮪﮫﮬﮭﮮ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
ﮯﮰﮱﯓﯔ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
ﯕﯖﯗﯘﯙ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
ﯟﯠﯡﯢﯣ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
ﯰﯱﯲﯳﯴﯵ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
ﭑﭒﭓﭔ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
ﭕﭖﭗﭘﭙ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ﭚﭛﭜﭝﭞ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
ﭟﭠﭡﭢﭣ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ﭩﭪﭫﭬﭭ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
ﭮﭯﭰﭱﭲ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﭳﭴﭵﭶﭷ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﭸﭹﭺﭻﭼ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
ﭽﭾﭿﮀ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
ﮁﮂﮃﮄﮅ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
ﮆﮇﮈﮉﮊ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
ﮋﮌﮍﮎﮏ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
ﮖﮗﮘﮙﮚ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
ﮛﮜﮝﮞﮟ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
ﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
ﯔﯕﯖﯗﯘﯙ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
ﯚﯛﯜﯝﯞﯟﯠ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
ﯡﯢﯣﯤﯥ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱﯲ
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
ﯳﯴﯵﯶﯷﯸ
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
ﯹﯺﯻﯼﯽ
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
ﯾﯿﰀﰁﰂ
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
ﭖﭗﭘ
አትገነዘቡምን?
ﭙﭚﭛﭜﭝ
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
ﭰﭱﭲﭳﭴ
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
ﭺﭻﭼﭽ
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
ﭾﭿﮀﮁﮂ
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
ﮐﮑﮒﮓ
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
ﮔﮕﮖﮗ
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
ﮘﮙﮚﮛ
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
ﮣﮤﮥﮦﮧ
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
ﮨﮩﮪﮫﮬﮭ
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
ﯕﯖﯗﯘ
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
ﯙﯚﯛﯜﯝ
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
ﯞﯟﯠﯡﯢ
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
ﯣﯤﯥﯦ
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
ﯧﯨﯩ
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
ﯱﯲﯳﯴﯵ
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
ﯶﯷﯸﯹ
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿﰀ
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
ﰁﰂﰃﰄ
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
ﰅﰆﰇﰈﰉ
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡

ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers