ሱረቱ አስ-ሳፋት ዐረቢ እና አማርኛ

ሱረቱ አስ-ሳፋትን ሙሉ አማርኛ ትርጉምና የድምፅ ቅኔ ጋር አንብቡ። ከአንቀጽ ወደ አንቀጽ ትርጉም። (182 አንቀጽ — مكية). አስ-ሳፋት ስሙ, አስ-ሳፋት ትርጉም, አስ-ሳፋት mp3, አስ-ሳፋት pdf.

ሱረቱ አስ-ሳፋትን አንብቡ እና ስሙ

🎧 አንቀጽ
M Mishary Rashid Alafasy
M Mahmoud Khalil Al-Husary
A Abdurrahman As-Sudais
M Mohamed Siddiq Al-Minshawi
A Abdul Basit Abdul Samad
A Ali Al-Hudhaify
A Ahmed ibn Ali al-Ajamy
A Abu Bakr Ash-Shaatree
M Muhammad Ayyoub
A Abdullah Basfar
A Abdullah Al-Juhani
M Maher Al Muaiqly
x1
وَالصَّافَّاتِ صَفًّا ۝١
📖 ትርጉም አንቀጽ 1
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
فَالزَّاجِرَاتِ زَجْرًا ۝٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 2
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
فَالتَّالِيَاتِ ذِكْرًا ۝٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 3
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
إِنَّ إِلَٰهَكُمْ لَوَاحِدٌ ۝٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 4
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا وَرَبُّ الْمَشَارِقِ ۝٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 5
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ ۝٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 6
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
وَحِفْظًا مِّن كُلِّ شَيْطَانٍ مَّارِدٍ ۝٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 7
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى الْمَلَإِ الْأَعْلَىٰ وَيُقْذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٍ ۝٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 8
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
دُحُورًا ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ وَاصِبٌ ۝٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 9
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
إِلَّا مَنْ خَطِفَ الْخَطْفَةَ فَأَتْبَعَهُ شِهَابٌ ثَاقِبٌ ۝١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 10
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
فَاسْتَفْتِهِمْ أَهُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَم مَّنْ خَلَقْنَا ۚ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّن طِينٍ لَّازِبٍ ۝١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 11
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
بَلْ عَجِبْتَ وَيَسْخَرُونَ ۝١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 12
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
وَإِذَا ذُكِّرُوا لَا يَذْكُرُونَ ۝١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 13
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
وَإِذَا رَأَوْا آيَةً يَسْتَسْخِرُونَ ۝١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 14
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
وَقَالُوا إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ ۝١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 15
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
أَإِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ ۝١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 16
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ ۝١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 17
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
قُلْ نَعَمْ وَأَنتُمْ دَاخِرُونَ ۝١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 18
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ فَإِذَا هُمْ يَنظُرُونَ ۝١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 19
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
وَقَالُوا يَا وَيْلَنَا هَٰذَا يَوْمُ الدِّينِ ۝٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 20
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ ۝٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 21
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
۞ احْشُرُوا الَّذِينَ ظَلَمُوا وَأَزْوَاجَهُمْ وَمَا كَانُوا يَعْبُدُونَ ۝٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 22
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
مِن دُونِ اللَّهِ فَاهْدُوهُمْ إِلَىٰ صِرَاطِ الْجَحِيمِ ۝٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 23
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
وَقِفُوهُمْ ۖ إِنَّهُم مَّسْئُولُونَ ۝٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 24
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
مَا لَكُمْ لَا تَنَاصَرُونَ ۝٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 25
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
بَلْ هُمُ الْيَوْمَ مُسْتَسْلِمُونَ ۝٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 26
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
وَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَاءَلُونَ ۝٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 27
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
قَالُوا إِنَّكُمْ كُنتُمْ تَأْتُونَنَا عَنِ الْيَمِينِ ۝٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 28
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
قَالُوا بَل لَّمْ تَكُونُوا مُؤْمِنِينَ ۝٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 29
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيْكُم مِّن سُلْطَانٍ ۖ بَلْ كُنتُمْ قَوْمًا طَاغِينَ ۝٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 30
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
فَحَقَّ عَلَيْنَا قَوْلُ رَبِّنَا ۖ إِنَّا لَذَائِقُونَ ۝٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 31
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
فَأَغْوَيْنَاكُمْ إِنَّا كُنَّا غَاوِينَ ۝٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 32
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
فَإِنَّهُمْ يَوْمَئِذٍ فِي الْعَذَابِ مُشْتَرِكُونَ ۝٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 33
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ ۝٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 34
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ ۝٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 35
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُو آلِهَتِنَا لِشَاعِرٍ مَّجْنُونٍ ۝٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 36
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
بَلْ جَاءَ بِالْحَقِّ وَصَدَّقَ الْمُرْسَلِينَ ۝٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 37
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
إِنَّكُمْ لَذَائِقُو الْعَذَابِ الْأَلِيمِ ۝٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 38
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
وَمَا تُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ ۝٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 39
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ ۝٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 40
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
أُولَٰئِكَ لَهُمْ رِزْقٌ مَّعْلُومٌ ۝٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 41
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
فَوَاكِهُ ۖ وَهُم مُّكْرَمُونَ ۝٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 42
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ ۝٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 43
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
عَلَىٰ سُرُرٍ مُّتَقَابِلِينَ ۝٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 44
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ ۝٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 45
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
بَيْضَاءَ لَذَّةٍ لِّلشَّارِبِينَ ۝٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 46
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ ۝٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 47
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
وَعِندَهُمْ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ عِينٌ ۝٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 48
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
كَأَنَّهُنَّ بَيْضٌ مَّكْنُونٌ ۝٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 49
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَاءَلُونَ ۝٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 50
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
قَالَ قَائِلٌ مِّنْهُمْ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٌ ۝٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 51
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
يَقُولُ أَإِنَّكَ لَمِنَ الْمُصَدِّقِينَ ۝٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 52
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
أَإِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَدِينُونَ ۝٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 53
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
قَالَ هَلْ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ ۝٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 54
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
فَاطَّلَعَ فَرَآهُ فِي سَوَاءِ الْجَحِيمِ ۝٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 55
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
قَالَ تَاللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرْدِينِ ۝٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 56
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
وَلَوْلَا نِعْمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ الْمُحْضَرِينَ ۝٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 57
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
أَفَمَا نَحْنُ بِمَيِّتِينَ ۝٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 58
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
إِلَّا مَوْتَتَنَا الْأُولَىٰ وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ ۝٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 59
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ ۝٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 60
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
لِمِثْلِ هَٰذَا فَلْيَعْمَلِ الْعَامِلُونَ ۝٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 61
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
أَذَٰلِكَ خَيْرٌ نُّزُلًا أَمْ شَجَرَةُ الزَّقُّومِ ۝٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 62
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
إِنَّا جَعَلْنَاهَا فِتْنَةً لِّلظَّالِمِينَ ۝٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 63
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
إِنَّهَا شَجَرَةٌ تَخْرُجُ فِي أَصْلِ الْجَحِيمِ ۝٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 64
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
طَلْعُهَا كَأَنَّهُ رُءُوسُ الشَّيَاطِينِ ۝٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 65
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
فَإِنَّهُمْ لَآكِلُونَ مِنْهَا فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ ۝٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 66
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّ لَهُمْ عَلَيْهَا لَشَوْبًا مِّنْ حَمِيمٍ ۝٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 67
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّ مَرْجِعَهُمْ لَإِلَى الْجَحِيمِ ۝٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 68
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
إِنَّهُمْ أَلْفَوْا آبَاءَهُمْ ضَالِّينَ ۝٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 69
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
فَهُمْ عَلَىٰ آثَارِهِمْ يُهْرَعُونَ ۝٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 70
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
وَلَقَدْ ضَلَّ قَبْلَهُمْ أَكْثَرُ الْأَوَّلِينَ ۝٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 71
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ ۝٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 72
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُنذَرِينَ ۝٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 73
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ ۝٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 74
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
وَلَقَدْ نَادَانَا نُوحٌ فَلَنِعْمَ الْمُجِيبُونَ ۝٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 75
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
وَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ ۝٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 76
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
وَجَعَلْنَا ذُرِّيَّتَهُ هُمُ الْبَاقِينَ ۝٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 77
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ ۝٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 78
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
سَلَامٌ عَلَىٰ نُوحٍ فِي الْعَالَمِينَ ۝٧٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 79
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝٨٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 80
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ ۝٨١
📖 ትርጉም አንቀጽ 81
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ ۝٨٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 82
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِ لَإِبْرَاهِيمَ ۝٨٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 83
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ ۝٨٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 84
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَاذَا تَعْبُدُونَ ۝٨٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 85
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
أَئِفْكًا آلِهَةً دُونَ اللَّهِ تُرِيدُونَ ۝٨٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 86
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ ۝٨٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 87
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
فَنَظَرَ نَظْرَةً فِي النُّجُومِ ۝٨٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 88
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٌ ۝٨٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 89
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
فَتَوَلَّوْا عَنْهُ مُدْبِرِينَ ۝٩٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 90
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
فَرَاغَ إِلَىٰ آلِهَتِهِمْ فَقَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ ۝٩١
📖 ትርጉም አንቀጽ 91
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
مَا لَكُمْ لَا تَنطِقُونَ ۝٩٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 92
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
فَرَاغَ عَلَيْهِمْ ضَرْبًا بِالْيَمِينِ ۝٩٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 93
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
فَأَقْبَلُوا إِلَيْهِ يَزِفُّونَ ۝٩٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 94
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
قَالَ أَتَعْبُدُونَ مَا تَنْحِتُونَ ۝٩٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 95
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
وَاللَّهُ خَلَقَكُمْ وَمَا تَعْمَلُونَ ۝٩٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 96
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
قَالُوا ابْنُوا لَهُ بُنْيَانًا فَأَلْقُوهُ فِي الْجَحِيمِ ۝٩٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 97
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
فَأَرَادُوا بِهِ كَيْدًا فَجَعَلْنَاهُمُ الْأَسْفَلِينَ ۝٩٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 98
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهْدِينِ ۝٩٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 99
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
رَبِّ هَبْ لِي مِنَ الصَّالِحِينَ ۝١٠٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 100
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
فَبَشَّرْنَاهُ بِغُلَامٍ حَلِيمٍ ۝١٠١
📖 ትርጉም አንቀጽ 101
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ السَّعْيَ قَالَ يَا بُنَيَّ إِنِّي أَرَىٰ فِي الْمَنَامِ أَنِّي أَذْبَحُكَ فَانظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَا أَبَتِ افْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِي إِن شَاءَ اللَّهُ مِنَ الصَّابِرِينَ ۝١٠٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 102
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
فَلَمَّا أَسْلَمَا وَتَلَّهُ لِلْجَبِينِ ۝١٠٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 103
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
وَنَادَيْنَاهُ أَن يَا إِبْرَاهِيمُ ۝١٠٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 104
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
قَدْ صَدَّقْتَ الرُّؤْيَا ۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝١٠٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 105
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْبَلَاءُ الْمُبِينُ ۝١٠٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 106
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
وَفَدَيْنَاهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ ۝١٠٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 107
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ ۝١٠٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 108
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
سَلَامٌ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ ۝١٠٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 109
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝١١٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 110
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ ۝١١١
📖 ትርጉም አንቀጽ 111
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
وَبَشَّرْنَاهُ بِإِسْحَاقَ نَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ ۝١١٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 112
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
وَبَارَكْنَا عَلَيْهِ وَعَلَىٰ إِسْحَاقَ ۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحْسِنٌ وَظَالِمٌ لِّنَفْسِهِ مُبِينٌ ۝١١٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 113
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
وَلَقَدْ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَارُونَ ۝١١٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 114
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
وَنَجَّيْنَاهُمَا وَقَوْمَهُمَا مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ ۝١١٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 115
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
وَنَصَرْنَاهُمْ فَكَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ ۝١١٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 116
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
وَآتَيْنَاهُمَا الْكِتَابَ الْمُسْتَبِينَ ۝١١٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 117
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
وَهَدَيْنَاهُمَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ ۝١١٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 118
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِمَا فِي الْآخِرِينَ ۝١١٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 119
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
سَلَامٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَارُونَ ۝١٢٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 120
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝١٢١
📖 ትርጉም አንቀጽ 121
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُمَا مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ ۝١٢٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 122
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ ۝١٢٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 123
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَلَا تَتَّقُونَ ۝١٢٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 124
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
أَتَدْعُونَ بَعْلًا وَتَذَرُونَ أَحْسَنَ الْخَالِقِينَ ۝١٢٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 125
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
اللَّهَ رَبَّكُمْ وَرَبَّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ ۝١٢٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 126
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ ۝١٢٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 127
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ ۝١٢٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 128
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ ۝١٢٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 129
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
سَلَامٌ عَلَىٰ إِلْ يَاسِينَ ۝١٣٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 130
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ ۝١٣١
📖 ትርጉም አንቀጽ 131
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ ۝١٣٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 132
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ الْمُرْسَلِينَ ۝١٣٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 133
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ نَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ ۝١٣٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 134
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ ۝١٣٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 135
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ ۝١٣٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 136
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
وَإِنَّكُمْ لَتَمُرُّونَ عَلَيْهِم مُّصْبِحِينَ ۝١٣٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 137
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
وَبِاللَّيْلِ ۗ أَفَلَا تَعْقِلُونَ ۝١٣٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 138
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ ۝١٣٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 139
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
إِذْ أَبَقَ إِلَى الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ ۝١٤٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 140
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ الْمُدْحَضِينَ ۝١٤١
📖 ትርጉም አንቀጽ 141
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
فَالْتَقَمَهُ الْحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٌ ۝١٤٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 142
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
فَلَوْلَا أَنَّهُ كَانَ مِنَ الْمُسَبِّحِينَ ۝١٤٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 143
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
لَلَبِثَ فِي بَطْنِهِ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ ۝١٤٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 144
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
۞ فَنَبَذْنَاهُ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ سَقِيمٌ ۝١٤٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 145
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
وَأَنبَتْنَا عَلَيْهِ شَجَرَةً مِّن يَقْطِينٍ ۝١٤٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 146
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
وَأَرْسَلْنَاهُ إِلَىٰ مِائَةِ أَلْفٍ أَوْ يَزِيدُونَ ۝١٤٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 147
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
فَآمَنُوا فَمَتَّعْنَاهُمْ إِلَىٰ حِينٍ ۝١٤٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 148
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
فَاسْتَفْتِهِمْ أَلِرَبِّكَ الْبَنَاتُ وَلَهُمُ الْبَنُونَ ۝١٤٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 149
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ ۝١٥٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 150
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
أَلَا إِنَّهُم مِّنْ إِفْكِهِمْ لَيَقُولُونَ ۝١٥١
📖 ትርጉም አንቀጽ 151
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ ۝١٥٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 152
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
أَصْطَفَى الْبَنَاتِ عَلَى الْبَنِينَ ۝١٥٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 153
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ ۝١٥٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 154
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ ۝١٥٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 155
አትገነዘቡምን?
أَمْ لَكُمْ سُلْطَانٌ مُّبِينٌ ۝١٥٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 156
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
فَأْتُوا بِكِتَابِكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ ۝١٥٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 157
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
وَجَعَلُوا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجِنَّةِ نَسَبًا ۚ وَلَقَدْ عَلِمَتِ الْجِنَّةُ إِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ ۝١٥٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 158
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ ۝١٥٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 159
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ ۝١٦٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 160
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
فَإِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ ۝١٦١
📖 ትርጉም አንቀጽ 161
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
مَا أَنتُمْ عَلَيْهِ بِفَاتِنِينَ ۝١٦٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 162
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
إِلَّا مَنْ هُوَ صَالِ الْجَحِيمِ ۝١٦٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 163
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
وَمَا مِنَّا إِلَّا لَهُ مَقَامٌ مَّعْلُومٌ ۝١٦٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 164
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
وَإِنَّا لَنَحْنُ الصَّافُّونَ ۝١٦٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 165
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
وَإِنَّا لَنَحْنُ الْمُسَبِّحُونَ ۝١٦٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 166
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
وَإِن كَانُوا لَيَقُولُونَ ۝١٦٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 167
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
لَوْ أَنَّ عِندَنَا ذِكْرًا مِّنَ الْأَوَّلِينَ ۝١٦٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 168
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
لَكُنَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ ۝١٦٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 169
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
فَكَفَرُوا بِهِ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ ۝١٧٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 170
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
وَلَقَدْ سَبَقَتْ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا الْمُرْسَلِينَ ۝١٧١
📖 ትርጉም አንቀጽ 171
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
إِنَّهُمْ لَهُمُ الْمَنصُورُونَ ۝١٧٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 172
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ الْغَالِبُونَ ۝١٧٣
📖 ትርጉም አንቀጽ 173
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
فَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ ۝١٧٤
📖 ትርጉም አንቀጽ 174
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
وَأَبْصِرْهُمْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ ۝١٧٥
📖 ትርጉም አንቀጽ 175
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ ۝١٧٦
📖 ትርጉም አንቀጽ 176
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمْ فَسَاءَ صَبَاحُ الْمُنذَرِينَ ۝١٧٧
📖 ትርጉም አንቀጽ 177
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
وَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ ۝١٧٨
📖 ትርጉም አንቀጽ 178
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
وَأَبْصِرْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ ۝١٧٩
📖 ትርጉም አንቀጽ 179
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ ۝١٨٠
📖 ትርጉም አንቀጽ 180
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ ۝١٨١
📖 ትርጉም አንቀጽ 181
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ ۝١٨٢
📖 ትርጉም አንቀጽ 182
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
← 36 አስ-ሳፋት (37/114) 38 →
ማንበብ ሱረቱ አስ-ሳፋት አማርኛ ትርጉም – ንባብ እና ድምፅ

37الصافات As-Saffat 📚 182 አንቀጽ مكية

ከቁጥር ወደ ቁጥር – ሱረቱ አስ-ሳፋት — 182 አንቀጽ




ቅዱስ ቁርኣን


Tuesday, August 18, 2026

Don't forget us in your sincere prayers