Surah Al-Waqiah with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Waqiah | الواقعة - Ayat Count 96 - The number of the surah in moshaf: 56 - The meaning of the surah in English: The Inevitable, The Event.

إِذَا وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ(1)

 መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡

لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ(2)

 ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡

خَافِضَةٌ رَّافِعَةٌ(3)

 ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡

إِذَا رُجَّتِ الْأَرْضُ رَجًّا(4)

 ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡

وَبُسَّتِ الْجِبَالُ بَسًّا(5)

 ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡

فَكَانَتْ هَبَاءً مُّنبَثًّا(6)

 የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ

وَكُنتُمْ أَزْوَاجًا ثَلَاثَةً(7)

 ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

فَأَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ(8)

 የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ(9)

 የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

وَالسَّابِقُونَ السَّابِقُونَ(10)

 (ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡

أُولَٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ(11)

 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡

فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ(12)

 በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ(13)

 ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَقَلِيلٌ مِّنَ الْآخِرِينَ(14)

 ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡

عَلَىٰ سُرُرٍ مَّوْضُونَةٍ(15)

 በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

مُّتَّكِئِينَ عَلَيْهَا مُتَقَابِلِينَ(16)

 በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡

يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ(17)

 በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ(18)

 ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ(19)

 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡

وَفَاكِهَةٍ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ(20)

 ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡

وَلَحْمِ طَيْرٍ مِّمَّا يَشْتَهُونَ(21)

 ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡

وَحُورٌ عِينٌ(22)

 ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡

كَأَمْثَالِ اللُّؤْلُؤِ الْمَكْنُونِ(23)

 ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡

جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ(24)

 በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا تَأْثِيمًا(25)

 በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡

إِلَّا قِيلًا سَلَامًا سَلَامًا(26)

 ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡

وَأَصْحَابُ الْيَمِينِ مَا أَصْحَابُ الْيَمِينِ(27)

 የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!

فِي سِدْرٍ مَّخْضُودٍ(28)

 በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡

وَطَلْحٍ مَّنضُودٍ(29)

 (ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡

وَظِلٍّ مَّمْدُودٍ(30)

 በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡

وَمَاءٍ مَّسْكُوبٍ(31)

 በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡

وَفَاكِهَةٍ كَثِيرَةٍ(32)

 ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡

لَّا مَقْطُوعَةٍ وَلَا مَمْنُوعَةٍ(33)

 የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡

وَفُرُشٍ مَّرْفُوعَةٍ(34)

 ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡

إِنَّا أَنشَأْنَاهُنَّ إِنشَاءً(35)

 እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡

فَجَعَلْنَاهُنَّ أَبْكَارًا(36)

 ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡

عُرُبًا أَتْرَابًا(37)

 ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡

لِّأَصْحَابِ الْيَمِينِ(38)

 ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ(39)

 ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَثُلَّةٌ مِّنَ الْآخِرِينَ(40)

 ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الشِّمَالِ مَا أَصْحَابُ الشِّمَالِ(41)

 የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡

فِي سَمُومٍ وَحَمِيمٍ(42)

 በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡

وَظِلٍّ مِّن يَحْمُومٍ(43)

 ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

لَّا بَارِدٍ وَلَا كَرِيمٍ(44)

 ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡

إِنَّهُمْ كَانُوا قَبْلَ ذَٰلِكَ مُتْرَفِينَ(45)

 እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ(46)

 በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يَقُولُونَ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ(47)

 ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ(48)

 «የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

قُلْ إِنَّ الْأَوَّلِينَ وَالْآخِرِينَ(49)

 በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡

لَمَجْمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ(50)

 «በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّكُمْ أَيُّهَا الضَّالُّونَ الْمُكَذِّبُونَ(51)

 «ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!

لَآكِلُونَ مِن شَجَرٍ مِّن زَقُّومٍ(52)

 « ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡

فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ(53)

 «ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ عَلَيْهِ مِنَ الْحَمِيمِ(54)

 «በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ شُرْبَ الْهِيمِ(55)

 «የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»

هَٰذَا نُزُلُهُمْ يَوْمَ الدِّينِ(56)

 ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡

نَحْنُ خَلَقْنَاكُمْ فَلَوْلَا تُصَدِّقُونَ(57)

 እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ(58)

 (በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ(59)

 እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

نَحْنُ قَدَّرْنَا بَيْنَكُمُ الْمَوْتَ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ(60)

 እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ أَمْثَالَكُمْ وَنُنشِئَكُمْ فِي مَا لَا تَعْلَمُونَ(61)

 ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ النَّشْأَةَ الْأُولَىٰ فَلَوْلَا تَذَكَّرُونَ(62)

 የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تَحْرُثُونَ(63)

 የምትዘሩትንም አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَزْرَعُونَهُ أَمْ نَحْنُ الزَّارِعُونَ(64)

 እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ لَجَعَلْنَاهُ حُطَامًا فَظَلْتُمْ تَفَكَّهُونَ(65)

 ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡

إِنَّا لَمُغْرَمُونَ(66)

 «እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ(67)

 «በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡

أَفَرَأَيْتُمُ الْمَاءَ الَّذِي تَشْرَبُونَ(68)

 ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

أَأَنتُمْ أَنزَلْتُمُوهُ مِنَ الْمُزْنِ أَمْ نَحْنُ الْمُنزِلُونَ(69)

 እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ جَعَلْنَاهُ أُجَاجًا فَلَوْلَا تَشْكُرُونَ(70)

 ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?

أَفَرَأَيْتُمُ النَّارَ الَّتِي تُورُونَ(71)

 ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

أَأَنتُمْ أَنشَأْتُمْ شَجَرَتَهَا أَمْ نَحْنُ الْمُنشِئُونَ(72)

 እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

نَحْنُ جَعَلْنَاهَا تَذْكِرَةً وَمَتَاعًا لِّلْمُقْوِينَ(73)

 እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ(74)

 የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

۞ فَلَا أُقْسِمُ بِمَوَاقِعِ النُّجُومِ(75)

 በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡

وَإِنَّهُ لَقَسَمٌ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ(76)

 እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡

إِنَّهُ لَقُرْآنٌ كَرِيمٌ(77)

 እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

فِي كِتَابٍ مَّكْنُونٍ(78)

 በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡

لَّا يَمَسُّهُ إِلَّا الْمُطَهَّرُونَ(79)

 የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡

تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ(80)

 ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

أَفَبِهَٰذَا الْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ(81)

 በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ(82)

 ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?

فَلَوْلَا إِذَا بَلَغَتِ الْحُلْقُومَ(83)

 (ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡

وَأَنتُمْ حِينَئِذٍ تَنظُرُونَ(84)

 እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنكُمْ وَلَٰكِن لَّا تُبْصِرُونَ(85)

 እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡

فَلَوْلَا إِن كُنتُمْ غَيْرَ مَدِينِينَ(86)

 የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡

تَرْجِعُونَهَا إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ(87)

 እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡

فَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُقَرَّبِينَ(88)

 (ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡

فَرَوْحٌ وَرَيْحَانٌ وَجَنَّتُ نَعِيمٍ(89)

 (ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ(90)

 ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡

فَسَلَامٌ لَّكَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ(91)

 ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُكَذِّبِينَ الضَّالِّينَ(92)

 ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡

فَنُزُلٌ مِّنْ حَمِيمٍ(93)

 ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡

وَتَصْلِيَةُ جَحِيمٍ(94)

 በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ الْيَقِينِ(95)

 ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ(96)

 የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah Al-Waqiah with the voice of the most famous Quran reciters :

surah Al-Waqiah mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter Al-Waqiah Complete with high quality
surah Al-Waqiah Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah Al-Waqiah Bandar Balila
Bandar Balila
surah Al-Waqiah Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah Al-Waqiah Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah Al-Waqiah Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah Al-Waqiah Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah Al-Waqiah Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah Al-Waqiah Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah Al-Waqiah Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah Al-Waqiah Fares Abbad
Fares Abbad
surah Al-Waqiah Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah Al-Waqiah Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah Al-Waqiah Al Hosary
Al Hosary
surah Al-Waqiah Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah Al-Waqiah Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب