Vakıa suresi çevirisi Amharca

  1. Suresi mp3
  2. Başka bir sure
  3. Amharca
Kuranı Kerim türkçe meali | Kur'an çevirileri | Amharca dili | Vakıa Suresi | الواقعة - Ayet sayısı 96 - Moshaf'taki surenin numarası: 56 - surenin ingilizce anlamı: The Inevitable, The Event.

إِذَا وَقَعَتِ الْوَاقِعَةُ(1)

 መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡

لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ(2)

 ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡

خَافِضَةٌ رَّافِعَةٌ(3)

 ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡

إِذَا رُجَّتِ الْأَرْضُ رَجًّا(4)

 ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡

وَبُسَّتِ الْجِبَالُ بَسًّا(5)

 ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡

فَكَانَتْ هَبَاءً مُّنبَثًّا(6)

 የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ

وَكُنتُمْ أَزْوَاجًا ثَلَاثَةً(7)

 ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

فَأَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَيْمَنَةِ(8)

 የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ مَا أَصْحَابُ الْمَشْأَمَةِ(9)

 የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

وَالسَّابِقُونَ السَّابِقُونَ(10)

 (ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡

أُولَٰئِكَ الْمُقَرَّبُونَ(11)

 እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡

فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ(12)

 በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ(13)

 ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَقَلِيلٌ مِّنَ الْآخِرِينَ(14)

 ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡

عَلَىٰ سُرُرٍ مَّوْضُونَةٍ(15)

 በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

مُّتَّكِئِينَ عَلَيْهَا مُتَقَابِلِينَ(16)

 በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡

يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ(17)

 በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ(18)

 ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ(19)

 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡

وَفَاكِهَةٍ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ(20)

 ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡

وَلَحْمِ طَيْرٍ مِّمَّا يَشْتَهُونَ(21)

 ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡

وَحُورٌ عِينٌ(22)

 ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡

كَأَمْثَالِ اللُّؤْلُؤِ الْمَكْنُونِ(23)

 ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡

جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ(24)

 በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

لَا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًا وَلَا تَأْثِيمًا(25)

 በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡

إِلَّا قِيلًا سَلَامًا سَلَامًا(26)

 ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡

وَأَصْحَابُ الْيَمِينِ مَا أَصْحَابُ الْيَمِينِ(27)

 የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!

فِي سِدْرٍ مَّخْضُودٍ(28)

 በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡

وَطَلْحٍ مَّنضُودٍ(29)

 (ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡

وَظِلٍّ مَّمْدُودٍ(30)

 በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡

وَمَاءٍ مَّسْكُوبٍ(31)

 በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡

وَفَاكِهَةٍ كَثِيرَةٍ(32)

 ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡

لَّا مَقْطُوعَةٍ وَلَا مَمْنُوعَةٍ(33)

 የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡

وَفُرُشٍ مَّرْفُوعَةٍ(34)

 ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡

إِنَّا أَنشَأْنَاهُنَّ إِنشَاءً(35)

 እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡

فَجَعَلْنَاهُنَّ أَبْكَارًا(36)

 ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡

عُرُبًا أَتْرَابًا(37)

 ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡

لِّأَصْحَابِ الْيَمِينِ(38)

 ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡

ثُلَّةٌ مِّنَ الْأَوَّلِينَ(39)

 ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَثُلَّةٌ مِّنَ الْآخِرِينَ(40)

 ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

وَأَصْحَابُ الشِّمَالِ مَا أَصْحَابُ الشِّمَالِ(41)

 የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡

فِي سَمُومٍ وَحَمِيمٍ(42)

 በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡

وَظِلٍّ مِّن يَحْمُومٍ(43)

 ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

لَّا بَارِدٍ وَلَا كَرِيمٍ(44)

 ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡

إِنَّهُمْ كَانُوا قَبْلَ ذَٰلِكَ مُتْرَفِينَ(45)

 እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يُصِرُّونَ عَلَى الْحِنثِ الْعَظِيمِ(46)

 በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

وَكَانُوا يَقُولُونَ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ(47)

 ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ(48)

 «የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

قُلْ إِنَّ الْأَوَّلِينَ وَالْآخِرِينَ(49)

 በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡

لَمَجْمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَاتِ يَوْمٍ مَّعْلُومٍ(50)

 «በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّكُمْ أَيُّهَا الضَّالُّونَ الْمُكَذِّبُونَ(51)

 «ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!

لَآكِلُونَ مِن شَجَرٍ مِّن زَقُّومٍ(52)

 « ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡

فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ(53)

 «ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ عَلَيْهِ مِنَ الْحَمِيمِ(54)

 «በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡

فَشَارِبُونَ شُرْبَ الْهِيمِ(55)

 «የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»

هَٰذَا نُزُلُهُمْ يَوْمَ الدِّينِ(56)

 ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡

نَحْنُ خَلَقْنَاكُمْ فَلَوْلَا تُصَدِّقُونَ(57)

 እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ(58)

 (በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ(59)

 እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

نَحْنُ قَدَّرْنَا بَيْنَكُمُ الْمَوْتَ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ(60)

 እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

عَلَىٰ أَن نُّبَدِّلَ أَمْثَالَكُمْ وَنُنشِئَكُمْ فِي مَا لَا تَعْلَمُونَ(61)

 ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ النَّشْأَةَ الْأُولَىٰ فَلَوْلَا تَذَكَّرُونَ(62)

 የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

أَفَرَأَيْتُم مَّا تَحْرُثُونَ(63)

 የምትዘሩትንም አያችሁን?

أَأَنتُمْ تَزْرَعُونَهُ أَمْ نَحْنُ الزَّارِعُونَ(64)

 እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ لَجَعَلْنَاهُ حُطَامًا فَظَلْتُمْ تَفَكَّهُونَ(65)

 ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡

إِنَّا لَمُغْرَمُونَ(66)

 «እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡

بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ(67)

 «በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡

أَفَرَأَيْتُمُ الْمَاءَ الَّذِي تَشْرَبُونَ(68)

 ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

أَأَنتُمْ أَنزَلْتُمُوهُ مِنَ الْمُزْنِ أَمْ نَحْنُ الْمُنزِلُونَ(69)

 እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

لَوْ نَشَاءُ جَعَلْنَاهُ أُجَاجًا فَلَوْلَا تَشْكُرُونَ(70)

 ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?

أَفَرَأَيْتُمُ النَّارَ الَّتِي تُورُونَ(71)

 ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

أَأَنتُمْ أَنشَأْتُمْ شَجَرَتَهَا أَمْ نَحْنُ الْمُنشِئُونَ(72)

 እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

نَحْنُ جَعَلْنَاهَا تَذْكِرَةً وَمَتَاعًا لِّلْمُقْوِينَ(73)

 እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ(74)

 የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡

۞ فَلَا أُقْسِمُ بِمَوَاقِعِ النُّجُومِ(75)

 በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡

وَإِنَّهُ لَقَسَمٌ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ(76)

 እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡

إِنَّهُ لَقُرْآنٌ كَرِيمٌ(77)

 እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

فِي كِتَابٍ مَّكْنُونٍ(78)

 በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡

لَّا يَمَسُّهُ إِلَّا الْمُطَهَّرُونَ(79)

 የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡

تَنزِيلٌ مِّن رَّبِّ الْعَالَمِينَ(80)

 ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

أَفَبِهَٰذَا الْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ(81)

 በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?

وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ(82)

 ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?

فَلَوْلَا إِذَا بَلَغَتِ الْحُلْقُومَ(83)

 (ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡

وَأَنتُمْ حِينَئِذٍ تَنظُرُونَ(84)

 እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنكُمْ وَلَٰكِن لَّا تُبْصِرُونَ(85)

 እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡

فَلَوْلَا إِن كُنتُمْ غَيْرَ مَدِينِينَ(86)

 የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡

تَرْجِعُونَهَا إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ(87)

 እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡

فَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُقَرَّبِينَ(88)

 (ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡

فَرَوْحٌ وَرَيْحَانٌ وَجَنَّتُ نَعِيمٍ(89)

 (ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ(90)

 ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡

فَسَلَامٌ لَّكَ مِنْ أَصْحَابِ الْيَمِينِ(91)

 ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡

وَأَمَّا إِن كَانَ مِنَ الْمُكَذِّبِينَ الضَّالِّينَ(92)

 ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡

فَنُزُلٌ مِّنْ حَمِيمٍ(93)

 ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡

وَتَصْلِيَةُ جَحِيمٍ(94)

 በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ الْيَقِينِ(95)

 ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡

فَسَبِّحْ بِاسْمِ رَبِّكَ الْعَظِيمِ(96)

 የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡


Amharca diğer sureler:

Bakara suresi Âl-i İmrân Nisâ suresi
Mâide suresi Yûsuf suresi İbrâhîm suresi
Hicr suresi Kehf suresi Meryem suresi
Hac suresi Kasas suresi Ankebût suresi
As-Sajdah Yâsîn suresi Duhân suresi
fetih suresi Hucurât suresi Kâf suresi
Necm suresi Rahmân suresi vakıa suresi
Haşr suresi Mülk suresi Hâkka suresi
İnşikâk suresi Alâ suresi Gâşiye suresi

En ünlü okuyucuların sesiyle Vakıa Suresi indirin:

Surah Al-Waqiah mp3: yüksek kalitede dinlemek ve indirmek için okuyucuyu seçerek
Vakıa Suresi Ahmed El Agamy
Ahmed El Agamy
Vakıa Suresi Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
Vakıa Suresi Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
Vakıa Suresi Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
Vakıa Suresi Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
Vakıa Suresi Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
Vakıa Suresi Ali Al Hudhaifi
Ali Al Hudhaifi
Vakıa Suresi Fares Abbad
Fares Abbad
Vakıa Suresi Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
Vakıa Suresi Muhammad Jibril
Muhammad Jibril
Vakıa Suresi Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
Vakıa Suresi Al Hosary
Al Hosary
Vakıa Suresi Al-afasi
Mishari Al-afasi
Vakıa Suresi Nasser Al Qatami
Nasser Al Qatami
Vakıa Suresi Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Sunday, May 19, 2024

Bizim için dua et, teşekkürler