Surah As-Saaffat with Amharic

  1. Surah mp3
  2. More
  3. Amharic
The Holy Quran | Quran translation | Language Amharic | Surah Assaaffat | الصافات - Ayat Count 182 - The number of the surah in moshaf: 37 - The meaning of the surah in English: Those Who Set The Ranks.

وَالصَّافَّاتِ صَفًّا(1)

 መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡

فَالزَّاجِرَاتِ زَجْرًا(2)

 መገሠጽንም በሚገሥጹት፤

فَالتَّالِيَاتِ ذِكْرًا(3)

 ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡

إِنَّ إِلَٰهَكُمْ لَوَاحِدٌ(4)

 አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا وَرَبُّ الْمَشَارِقِ(5)

 የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ(6)

 እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡

وَحِفْظًا مِّن كُلِّ شَيْطَانٍ مَّارِدٍ(7)

 አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى الْمَلَإِ الْأَعْلَىٰ وَيُقْذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٍ(8)

 ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡

دُحُورًا ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ وَاصِبٌ(9)

 የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

إِلَّا مَنْ خَطِفَ الْخَطْفَةَ فَأَتْبَعَهُ شِهَابٌ ثَاقِبٌ(10)

 ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

فَاسْتَفْتِهِمْ أَهُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَم مَّنْ خَلَقْنَا ۚ إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّن طِينٍ لَّازِبٍ(11)

 ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡

بَلْ عَجِبْتَ وَيَسْخَرُونَ(12)

 ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡

وَإِذَا ذُكِّرُوا لَا يَذْكُرُونَ(13)

 በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡

وَإِذَا رَأَوْا آيَةً يَسْتَسْخِرُونَ(14)

 ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

وَقَالُوا إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ(15)

 ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

أَإِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ(16)

 «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ(17)

 «የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡

قُلْ نَعَمْ وَأَنتُمْ دَاخِرُونَ(18)

 «አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ فَإِذَا هُمْ يَنظُرُونَ(19)

 እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

وَقَالُوا يَا وَيْلَنَا هَٰذَا يَوْمُ الدِّينِ(20)

 «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

هَٰذَا يَوْمُ الْفَصْلِ الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ(21)

 «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

۞ احْشُرُوا الَّذِينَ ظَلَمُوا وَأَزْوَاجَهُمْ وَمَا كَانُوا يَعْبُدُونَ(22)

 (ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

مِن دُونِ اللَّهِ فَاهْدُوهُمْ إِلَىٰ صِرَاطِ الْجَحِيمِ(23)

 «ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡

وَقِفُوهُمْ ۖ إِنَّهُم مَّسْئُولُونَ(24)

 «አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡

مَا لَكُمْ لَا تَنَاصَرُونَ(25)

 (ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡

بَلْ هُمُ الْيَوْمَ مُسْتَسْلِمُونَ(26)

 በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

وَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَاءَلُونَ(27)

 የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

قَالُوا إِنَّكُمْ كُنتُمْ تَأْتُونَنَا عَنِ الْيَمِينِ(28)

 (ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

قَالُوا بَل لَّمْ تَكُونُوا مُؤْمِنِينَ(29)

 (አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيْكُم مِّن سُلْطَانٍ ۖ بَلْ كُنتُمْ قَوْمًا طَاغِينَ(30)

 «ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

فَحَقَّ عَلَيْنَا قَوْلُ رَبِّنَا ۖ إِنَّا لَذَائِقُونَ(31)

 «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡

فَأَغْوَيْنَاكُمْ إِنَّا كُنَّا غَاوِينَ(32)

 «ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

فَإِنَّهُمْ يَوْمَئِذٍ فِي الْعَذَابِ مُشْتَرِكُونَ(33)

 ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ(34)

 እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ(35)

 እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡

وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُو آلِهَتِنَا لِشَاعِرٍ مَّجْنُونٍ(36)

 እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

بَلْ جَاءَ بِالْحَقِّ وَصَدَّقَ الْمُرْسَلِينَ(37)

 አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡

إِنَّكُمْ لَذَائِقُو الْعَذَابِ الْأَلِيمِ(38)

 እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

وَمَا تُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ(39)

 ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡

إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ(40)

 ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡

أُولَٰئِكَ لَهُمْ رِزْقٌ مَّعْلُومٌ(41)

 እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡

فَوَاكِهُ ۖ وَهُم مُّكْرَمُونَ(42)

 ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤

فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ(43)

 በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡

عَلَىٰ سُرُرٍ مُّتَقَابِلِينَ(44)

 ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ(45)

 ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡

بَيْضَاءَ لَذَّةٍ لِّلشَّارِبِينَ(46)

 ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ(47)

 በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡

وَعِندَهُمْ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ عِينٌ(48)

 እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡

كَأَنَّهُنَّ بَيْضٌ مَّكْنُونٌ(49)

 እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَسَاءَلُونَ(50)

 የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡

قَالَ قَائِلٌ مِّنْهُمْ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٌ(51)

 ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡

يَقُولُ أَإِنَّكَ لَمِنَ الْمُصَدِّقِينَ(52)

 «በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

أَإِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَإِنَّا لَمَدِينُونَ(53)

 «በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡

قَالَ هَلْ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ(54)

 እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

فَاطَّلَعَ فَرَآهُ فِي سَوَاءِ الْجَحِيمِ(55)

 ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

قَالَ تَاللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرْدِينِ(56)

 ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

وَلَوْلَا نِعْمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ الْمُحْضَرِينَ(57)

 «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»

أَفَمَا نَحْنُ بِمَيِّتِينَ(58)

 (የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

إِلَّا مَوْتَتَنَا الْأُولَىٰ وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ(59)

 «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ(60)

 ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

لِمِثْلِ هَٰذَا فَلْيَعْمَلِ الْعَامِلُونَ(61)

 ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡

أَذَٰلِكَ خَيْرٌ نُّزُلًا أَمْ شَجَرَةُ الزَّقُّومِ(62)

 በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

إِنَّا جَعَلْنَاهَا فِتْنَةً لِّلظَّالِمِينَ(63)

 እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

إِنَّهَا شَجَرَةٌ تَخْرُجُ فِي أَصْلِ الْجَحِيمِ(64)

 እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡

طَلْعُهَا كَأَنَّهُ رُءُوسُ الشَّيَاطِينِ(65)

 እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

فَإِنَّهُمْ لَآكِلُونَ مِنْهَا فَمَالِئُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ(66)

 እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّ لَهُمْ عَلَيْهَا لَشَوْبًا مِّنْ حَمِيمٍ(67)

 ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

ثُمَّ إِنَّ مَرْجِعَهُمْ لَإِلَى الْجَحِيمِ(68)

 ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡

إِنَّهُمْ أَلْفَوْا آبَاءَهُمْ ضَالِّينَ(69)

 እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡

فَهُمْ عَلَىٰ آثَارِهِمْ يُهْرَعُونَ(70)

 እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

وَلَقَدْ ضَلَّ قَبْلَهُمْ أَكْثَرُ الْأَوَّلِينَ(71)

 ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡

وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ(72)

 በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُنذَرِينَ(73)

 የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡

إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ(74)

 ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

وَلَقَدْ نَادَانَا نُوحٌ فَلَنِعْمَ الْمُجِيبُونَ(75)

 ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

وَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ(76)

 እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡

وَجَعَلْنَا ذُرِّيَّتَهُ هُمُ الْبَاقِينَ(77)

 ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤

وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ(78)

 በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

سَلَامٌ عَلَىٰ نُوحٍ فِي الْعَالَمِينَ(79)

 «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(80)

 እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ(81)

 እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡

ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ(82)

 ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِ لَإِبْرَاهِيمَ(83)

 ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡

إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ(84)

 ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَاذَا تَعْبُدُونَ(85)

 «ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

أَئِفْكًا آلِهَةً دُونَ اللَّهِ تُرِيدُونَ(86)

 «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ(87)

 «በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡

فَنَظَرَ نَظْرَةً فِي النُّجُومِ(88)

 በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡

فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٌ(89)

 «እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡

فَتَوَلَّوْا عَنْهُ مُدْبِرِينَ(90)

 ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

فَرَاغَ إِلَىٰ آلِهَتِهِمْ فَقَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ(91)

 ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»

مَا لَكُمْ لَا تَنطِقُونَ(92)

 «የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»

فَرَاغَ عَلَيْهِمْ ضَرْبًا بِالْيَمِينِ(93)

 በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡

فَأَقْبَلُوا إِلَيْهِ يَزِفُّونَ(94)

 ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡

قَالَ أَتَعْبُدُونَ مَا تَنْحِتُونَ(95)

 አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»

وَاللَّهُ خَلَقَكُمْ وَمَا تَعْمَلُونَ(96)

 «አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

قَالُوا ابْنُوا لَهُ بُنْيَانًا فَأَلْقُوهُ فِي الْجَحِيمِ(97)

 «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

فَأَرَادُوا بِهِ كَيْدًا فَجَعَلْنَاهُمُ الْأَسْفَلِينَ(98)

 በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهْدِينِ(99)

 አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»

رَبِّ هَبْ لِي مِنَ الصَّالِحِينَ(100)

 ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡

فَبَشَّرْنَاهُ بِغُلَامٍ حَلِيمٍ(101)

 ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡

فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ السَّعْيَ قَالَ يَا بُنَيَّ إِنِّي أَرَىٰ فِي الْمَنَامِ أَنِّي أَذْبَحُكَ فَانظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَا أَبَتِ افْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِي إِن شَاءَ اللَّهُ مِنَ الصَّابِرِينَ(102)

 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡

فَلَمَّا أَسْلَمَا وَتَلَّهُ لِلْجَبِينِ(103)

 ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡

وَنَادَيْنَاهُ أَن يَا إِبْرَاهِيمُ(104)

 ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

قَدْ صَدَّقْتَ الرُّؤْيَا ۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(105)

 ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْبَلَاءُ الْمُبِينُ(106)

 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡

وَفَدَيْنَاهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ(107)

 በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡

وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ(108)

 በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡

سَلَامٌ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ(109)

 ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡

كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(110)

 እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ(111)

 እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡

وَبَشَّرْنَاهُ بِإِسْحَاقَ نَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ(112)

 በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

وَبَارَكْنَا عَلَيْهِ وَعَلَىٰ إِسْحَاقَ ۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحْسِنٌ وَظَالِمٌ لِّنَفْسِهِ مُبِينٌ(113)

 በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡

وَلَقَدْ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَارُونَ(114)

 በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡

وَنَجَّيْنَاهُمَا وَقَوْمَهُمَا مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ(115)

 እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡

وَنَصَرْنَاهُمْ فَكَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ(116)

 ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡

وَآتَيْنَاهُمَا الْكِتَابَ الْمُسْتَبِينَ(117)

 በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡

وَهَدَيْنَاهُمَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ(118)

 ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡

وَتَرَكْنَا عَلَيْهِمَا فِي الْآخِرِينَ(119)

 በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡

سَلَامٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَارُونَ(120)

 ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(121)

 እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُمَا مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ(122)

 ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡

وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ(123)

 ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَلَا تَتَّقُونَ(124)

 ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?

أَتَدْعُونَ بَعْلًا وَتَذَرُونَ أَحْسَنَ الْخَالِقِينَ(125)

 በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?

اللَّهَ رَبَّكُمْ وَرَبَّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ(126)

 አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?

فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ(127)

 አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡

إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ(128)

 ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ(129)

 በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡

سَلَامٌ عَلَىٰ إِلْ يَاسِينَ(130)

 ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ(131)

 እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ(132)

 እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡

وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ الْمُرْسَلِينَ(133)

 ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذْ نَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ(134)

 እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ(135)

 (በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡

ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ(136)

 ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

وَإِنَّكُمْ لَتَمُرُّونَ عَلَيْهِم مُّصْبِحِينَ(137)

 እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡

وَبِاللَّيْلِ ۗ أَفَلَا تَعْقِلُونَ(138)

 በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?

وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ(139)

 ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

إِذْ أَبَقَ إِلَى الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ(140)

 ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡

فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ الْمُدْحَضِينَ(141)

 ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡

فَالْتَقَمَهُ الْحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٌ(142)

 እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

فَلَوْلَا أَنَّهُ كَانَ مِنَ الْمُسَبِّحِينَ(143)

 እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤

لَلَبِثَ فِي بَطْنِهِ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ(144)

 እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡

۞ فَنَبَذْنَاهُ بِالْعَرَاءِ وَهُوَ سَقِيمٌ(145)

 እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡

وَأَنبَتْنَا عَلَيْهِ شَجَرَةً مِّن يَقْطِينٍ(146)

 በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

وَأَرْسَلْنَاهُ إِلَىٰ مِائَةِ أَلْفٍ أَوْ يَزِيدُونَ(147)

 ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡

فَآمَنُوا فَمَتَّعْنَاهُمْ إِلَىٰ حِينٍ(148)

 አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡

فَاسْتَفْتِهِمْ أَلِرَبِّكَ الْبَنَاتُ وَلَهُمُ الْبَنُونَ(149)

 (የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ(150)

 ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?

أَلَا إِنَّهُم مِّنْ إِفْكِهِمْ لَيَقُولُونَ(151)

 ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-

وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ(152)

 «አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡

أَصْطَفَى الْبَنَاتِ عَلَى الْبَنِينَ(153)

 በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?

مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ(154)

 ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

أَفَلَا تَذَكَّرُونَ(155)

 አትገነዘቡምን?

أَمْ لَكُمْ سُلْطَانٌ مُّبِينٌ(156)

 ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?

فَأْتُوا بِكِتَابِكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ(157)

 «እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

وَجَعَلُوا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجِنَّةِ نَسَبًا ۚ وَلَقَدْ عَلِمَتِ الْجِنَّةُ إِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ(158)

 በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡

سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ(159)

 አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡

إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ(160)

 ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡

فَإِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ(161)

 እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤

مَا أَنتُمْ عَلَيْهِ بِفَاتِنِينَ(162)

 በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡

إِلَّا مَنْ هُوَ صَالِ الْجَحِيمِ(163)

 ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

وَمَا مِنَّا إِلَّا لَهُ مَقَامٌ مَّعْلُومٌ(164)

 (ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡

وَإِنَّا لَنَحْنُ الصَّافُّونَ(165)

 እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡

وَإِنَّا لَنَحْنُ الْمُسَبِّحُونَ(166)

 እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡

وَإِن كَانُوا لَيَقُولُونَ(167)

 እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

لَوْ أَنَّ عِندَنَا ذِكْرًا مِّنَ الْأَوَّلِينَ(168)

 «ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤

لَكُنَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ(169)

 «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»

فَكَفَرُوا بِهِ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ(170)

 ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

وَلَقَدْ سَبَقَتْ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا الْمُرْسَلِينَ(171)

 (የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡

إِنَّهُمْ لَهُمُ الْمَنصُورُونَ(172)

 እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ الْغَالِبُونَ(173)

 ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

فَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ(174)

 ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡

وَأَبْصِرْهُمْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ(175)

 እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡

أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ(176)

 በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمْ فَسَاءَ صَبَاحُ الْمُنذَرِينَ(177)

 በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

وَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّىٰ حِينٍ(178)

 እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡

وَأَبْصِرْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ(179)

 ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡

سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ(180)

 የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡

وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ(181)

 በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤

وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ(182)

 ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡


More surahs in Amharic:


Al-Baqarah Al-'Imran An-Nisa'
Al-Ma'idah Yusuf Ibrahim
Al-Hijr Al-Kahf Maryam
Al-Hajj Al-Qasas Al-'Ankabut
As-Sajdah Ya Sin Ad-Dukhan
Al-Fath Al-Hujurat Qaf
An-Najm Ar-Rahman Al-Waqi'ah
Al-Hashr Al-Mulk Al-Haqqah
Al-Inshiqaq Al-A'la Al-Ghashiyah

Download surah As-Saaffat with the voice of the most famous Quran reciters :

surah As-Saaffat mp3 : choose the reciter to listen and download the chapter As-Saaffat Complete with high quality
surah As-Saaffat Ahmed El Agamy
Ahmed Al Ajmy
surah As-Saaffat Bandar Balila
Bandar Balila
surah As-Saaffat Khalid Al Jalil
Khalid Al Jalil
surah As-Saaffat Saad Al Ghamdi
Saad Al Ghamdi
surah As-Saaffat Saud Al Shuraim
Saud Al Shuraim
surah As-Saaffat Abdul Basit Abdul Samad
Abdul Basit
surah As-Saaffat Abdul Rashid Sufi
Abdul Rashid Sufi
surah As-Saaffat Abdullah Basfar
Abdullah Basfar
surah As-Saaffat Abdullah Awwad Al Juhani
Abdullah Al Juhani
surah As-Saaffat Fares Abbad
Fares Abbad
surah As-Saaffat Maher Al Muaiqly
Maher Al Muaiqly
surah As-Saaffat Muhammad Siddiq Al Minshawi
Al Minshawi
surah As-Saaffat Al Hosary
Al Hosary
surah As-Saaffat Al-afasi
Mishari Al-afasi
surah As-Saaffat Yasser Al Dosari
Yasser Al Dosari


Tuesday, May 7, 2024

لا تنسنا من دعوة صالحة بظهر الغيب